የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ፌኒቶይን መድኃኒት የጥራት ችግር አለበት በሚል በአስቸኳይ ከገበያ እንዲሰበሰብ አዘዘ

ፌኒቶይን
ፌኒቶይን  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.03.2026
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ፌኒቶይን መድኃኒት የጥራት ችግር አለበት በሚል በአስቸኳይ ከገበያ እንዲሰበሰብ አዘዘ

የአገልግሎቱ የባህር ዳር ቅርንጫፍ፤ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ በተባለ ኩባንያ የተመረቱ የፌኒቶይን 100 ሚሊ ግራም ታብሌት መድኃኒቶች በሙሉ የጥራት ጉድለት የታየባቸው በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲሰበሰቡ ለሁሉም የጤና ተቋማት ትዕዛዝ አስተላልፏል።

አገልግሎቱ መድኃኒቱን ያልመለሱ የጤና ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁ ጥብቅ ማሳሰቢያ መስጠቱን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎቱ አስጠንቅቋል።

ፌኒቶይን የሚጥል በሽታን ለመቆጣጠር የሚያገለግል መድኃኒት ነው።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0