የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደብረ ማርቆስ በረራ እንደሚጀምር አስታወቀ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.03.2026
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ደብረ ማርቆስ በረራ እንደሚጀምር አስታወቀ

አየር መንገዱ በሳምንት ሦስት ቀናት ማለትም በየሳምንቱ ማክሰኞ፣ ሐሙስ እና ቅዳሜ የአማራ ክልሏን ደብረ ማርቆስ ከተማ ከአዲስ አበባ ጋር በቀጥታ የሚያገናኝ ይሆናል።

ይህ አዲስ የበረራ መስመር ለደብረ ማርቆስና አካባቢው ማኅበረሰብ ፈጣን የትራንስፖርት አማራጭ ከመፍጠሩም በላይ ለንግድ፣ ለጤና አገልግሎት እና ለቅርስ ቱሪዝም ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።

ደብረ ማርቆስን ጨምሮ አየር መንገዱ በቅርቡ ይፋ ያደረጋቸው የነገሌ ቦረና እና የጎሬ መቱ በረራዎች ሲታከሉ፤ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹ ወደ 27 ከፍ እንደሚሉ ተመላክቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0