'ቆይቶ መሞት ወይም በህይወት ለመኖር መሰደድ' - ኢትዮጵያዊ ምሁር ስለ ኢራን የስደተኞች ጫና

ሰብስክራይብ

'ቆይቶ መሞት ወይም በህይወት ለመኖር መሰደድ' - ኢትዮጵያዊ ምሁር ስለ ኢራን የስደተኞች ጫና

የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት በመሠረተ ልማቶችና የኢኮኖሚ ስርዓቶች ላይ ስልታዊ ውድመት በማድረሱ ቀጣናዊ ቀውሱን በፍጥነት ወደ ዓለም አቀፍ የስደት ስጋት እየለወጠው መሆኑን የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁር አብዱ መሐመድ አሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ ግጭቱን ወደ መጠነ ሰፊ ስደት የሚቀይሩ መዋቅራዊ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦

የመሠረታዊ መዋቅሮች መፈራረስ፦ የመኖሪያ መንደሮች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ሆስፒታሎች፣ የኤሌክትሪክ እና የውሃ አቅርቦት መስመሮች መውደም፣

የከተማ አካባቢዎችን ኢላማ ማድረግ እና የጅምላ መልቀቂያ ትዕዛዞች፣

የኢኮኖሚ መናጋት፦ የአቪዬሽን፣ የቱሪዝም እና የኢነርጂ ኤክስፖርት ዘርፎች መፈራረስ ስደተኛ ሠራተኞችን እንዲፈናቀሉ ማድረጉ፣

የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መዳከም፦ የምግብ እና የመድኃኒት አቅርቦት መስመሮች መጥበብ ስደተኞች ለሁለተኛ ጊዜ እንዲሰደዱ ማስገደዱ፣

በአስተናጋጅ ሀገራት (እንደ ሊባኖስ እና ኢራን) ያለው አለመረጋጋት፦ ስደተኞችን የመርዳት አቅማቸው ከቁጥጥር በላይ መሆኑ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0