በጥብቅ የሕዝብ መሬቶች ላይ የንግድ ንብ ልማትን ለማስፋፋት የሚያግዝ ረቂቅ መመሪያ ለውይይት ቀረበ

ሰብስክራይብ
በጥብቅ የሕዝብ መሬቶች ላይ የንግድ ንብ ልማትን ለማስፋፋት የሚያግዝ ረቂቅ መመሪያ ለውይይት ቀረበ

ግብርና ሚኒስቴር ከዓለም አቀፍ የነፍሳት ሥነ-አካል እና ስነ-ምኅዳር ማዕከል ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እንደተደረገበት ግብርና ሚኒቴር አስታውቋል፡፡

በማኅበረሰብ ጥብቅ መሬቶች (ደኖች፣ ፓርኮች እና ሌሎች ቦታዎች) አካባቢ የሚገኙ ወጣቶች እና ሴቶች ቦታውን ከመጠበቅና ከመንከባከብ በተጨማሪ ከንብ ልማት ጋር አቀናጅተው በመሥራት ተጠቃሚ መሆን አለባቸው መባሉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በኢትዮጵያ ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመኖሩ ምክንያት በዓመት በአማካኝ 500 ሺህ ቶን ማር፣ 50 ሺህ ቶን የንብ ሰምና 500 ቶን የንብ ሙጫ የማምረት አቅም መኖሩ ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0