የየመን ሁቲዎች አሜሪካና እስራኤል ውጥረቱን የሚያባብሱ ከሆነ ከኢራን ወገን ሆነው ጦርነቱን እንደሚቀላቀሉ አስጠነቀቁ

ሰብስክራይብ

የየመን ሁቲዎች አሜሪካና እስራኤል ውጥረቱን የሚያባብሱ ከሆነ ከኢራን ወገን ሆነው ጦርነቱን እንደሚቀላቀሉ አስጠነቀቁ

​የሁቲ ቃል አቀባይ ያህያ ሳሪ ባወጡት ይፋዊ መግለጫ፣ ሁኔታው እየተባባሰ የሚቀጥል ከሆነ ንቅናቄው በኢራን ወገን ተሰልፎ ጦርነቱን ለመቀላቀል ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

  ጣልቃ ለመግባት የተቀመጡ ቅድመ ሁኔታዎች፦

◻ ማንኛውም አዲስ አገር ወይም ጥምረት በኢራንና በአጋሮቿ ላይ የሚፈፀመውን የአሜሪካና የእስራኤል ጥቃት የሚቀላቀል ከሆነ፤

◻ ቀይ ባሕር በኢራን ወይም በሌሎች የክልሉ አገራት ላይ ለሚሰነዘሩ ጥቃቶች እንደ መነሻ የሚያገለግል ከሆነ እና

◻ በኢራንና "የመቋቋም ዘንግ" በሚባሉት ላይ የሚሰነዘረው ጥቃት ተባብሶ የሚቀጥል ከሆነ።

​ ያህያ ሳሪ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱት ጦርነት "ፍትሐዊ ያልሆነ፣ ጨቋኝና ያለ ምንም ትንኮሳ የተፈጸመ ጥቃት" ነው ሲሉ ገልጸውታል። በተጨማሪም፣ ይህ ድርጊት የክልሉንና የዓለምን መረጋጋት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን አስጠንቅቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0