ሴኔጋል በአፍሪካ ዋንጫ የነበራት አሸናፊነት ቢሰረዝም፣ ዋንጫውን አስመልክታ ከፍተኛ አከባበር እንደምታዘጋጅ የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ
17:59 27.03.2026 (የተሻሻለ: 18:39 27.03.2026)

ሰብስክራይብ
ሴኔጋል በአፍሪካ ዋንጫ የነበራት አሸናፊነት ቢሰረዝም፣ ዋንጫውን አስመልክታ ከፍተኛ አከባበር እንደምታዘጋጅ የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ
ምንም እንኳን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሴኔጋልን አሸናፊነት ቢሰርዝም፣ የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ነገ ቅዳሜ በፓሪስ ከፔሩ ጋር ከሚያደርገው የወዳጅነት ጨዋታ አስቀድሞ የዋንጫ አውቶቡስ ጉዞ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የቴራንጋ አንበሶች ተብሎ የሚጠራው የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን ጥር 10 በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ አስተናጋጇን ሞሮኮን በጭማሪ ሰዓት 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስተው ነበር። ሆኖም ግን፣ በጨዋታው መጠናቀቂያ አካባቢ ለሞሮኮ የተሰጠውን የፍጹም ቅጣት ምት ተከትሎ የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳውን ለቀው በመውጣታቸውና በተፈጠረው ግርግር ምክንያት ካፍ ውጤቱን ሰርዞታል።
"በስፖርታችን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና ግልጽ የሆነ 'የአስተዳደር ዘረፋ' ቢፈጸምብንም … ሴኔጋል አትንበረከክም፤ በእሴቶቿም አትደራደርም" ሲሉ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ፋል በፓሪስ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ባለፈው ማክሰኞ የዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት የሴኔጋልን ይግባኝ መቀበሉን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ውሳኔውንም "በተቻለ ፍጥነት" እንደሚሰጥ ገልጿል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
ምንም እንኳን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) የሴኔጋልን አሸናፊነት ቢሰርዝም፣ የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን ነገ ቅዳሜ በፓሪስ ከፔሩ ጋር ከሚያደርገው የወዳጅነት ጨዋታ አስቀድሞ የዋንጫ አውቶቡስ ጉዞ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
የቴራንጋ አንበሶች ተብሎ የሚጠራው የሴኔጋል ብሄራዊ ቡድን ጥር 10 በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ አስተናጋጇን ሞሮኮን በጭማሪ ሰዓት 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን አንስተው ነበር። ሆኖም ግን፣ በጨዋታው መጠናቀቂያ አካባቢ ለሞሮኮ የተሰጠውን የፍጹም ቅጣት ምት ተከትሎ የሴኔጋል ተጫዋቾች ሜዳውን ለቀው በመውጣታቸውና በተፈጠረው ግርግር ምክንያት ካፍ ውጤቱን ሰርዞታል።
"በስፖርታችን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና ግልጽ የሆነ 'የአስተዳደር ዘረፋ' ቢፈጸምብንም … ሴኔጋል አትንበረከክም፤ በእሴቶቿም አትደራደርም" ሲሉ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላዬ ፋል በፓሪስ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ባለፈው ማክሰኞ የዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት የሴኔጋልን ይግባኝ መቀበሉን ያረጋገጠ ሲሆን፣ ውሳኔውንም "በተቻለ ፍጥነት" እንደሚሰጥ ገልጿል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X