የኢራን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ ከ600 በላይ ት/ት ቤቶች ሲወድሙ፣ ከ1,000 በላይ ተማሪዎችና መምህራን ተገድለዋል ወይም ቆስለዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

ሰብስክራይብ
የኢራን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ ከ600 በላይ ትምህርት ቤቶች ሲወድሙ፣ ከ1,000 በላይ ተማሪዎችና መምህራን ተገድለዋል ወይም ቆስለዋል - የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር

​በሚናብ፣ በሚገኘው ሻጃሬ ታዬቤህ ትምህርት ቤት ላይ የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ በተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፣ በኢራን ውስጥ በርካታ የማኅበራዊ መሠረተ ልማቶች መውደማቸውን ገልጸዋል።

​ እንደ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገለፃ፣ የአሜሪካ-እስራኤል ኃይሎች ሆስፒታሎችን፣ አምቡላንሶችን፣ የህክምና ባለሙያዎችን፣ የቀይ ጨረቃ ሰራተኞችን፣ የነዳጅ ማጣሪያዎችን፣ የውሃ ማጠራቀሚያዎችን እና የመኖሪያ አካባቢዎችን ደጋግመው በመምታት ሰብአዊ መብቶችን እና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን ስልታዊ በሆነ መንገድ ጥሰዋል።

​ኢራን፣ የተመድ እና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እነዚህን ግልጽ ጥቃቶች እንዲያወግዙ ያሳሰበች ሲሆን፣ አርጋቺ አክለውም ይህንን ወረራ ማውገዝ ግዴታ መሆኑን ገልጸዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0