ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ማላቦ ገቡ

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.03.2026
ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ11ኛው የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ማላቦ ገቡ

አየር ማረፊያ ሲደርሱም በኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ማኑኤል ኦሳ ንሱዌ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ከመጋቢት 18 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚካሄደው ጉባኤው፣ "የተሸጋገረ እና የታደሰ የአፍሪካ፣ ካሪቢያን እና ፓሲፊክ ሀገራት ድርጅት ለሁሉ አቀፍ፣ ዘላቂ እና በእምነት ላይ ለተመሰረተ ባለብዙ ወገን ግንኙነት" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል።

ይህ ጉባኤ ድርጅቱ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት የሚዘክር ሲሆን፣ 79 አባል ሀገራትን በማስተባበር በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ተፅዕኖ ለማሳደግ ያለመ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0