አንዳንድ ተንታኞች የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት መዘዝ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ሊነጻጸር እንደሚችል ተናግረዋል - ፑቲን
16:46 26.03.2026 (የተሻሻለ: 16:54 26.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አንዳንድ ተንታኞች የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት መዘዝ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ሊነጻጸር እንደሚችል ተናግረዋል - ፑቲን
በሩሲያ የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች እና ስራ ፈጣሪዎች ሕብረት ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ፑቲን የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አፅንዖት ሰጥተው ገልጸዋል፦
🟠 አሁን ያለውን የዓለም ሁኔታ ተጠቅሞ ከፍተኛ ትርፍን ብቻ የመሰብሰብ ፍላጎት ሊኖር ቢችልም፣ ኩባንያዎች ግን ራሳቸውን ማቀብ ይኖርባቸዋል።
🟠 ሩሲያ አሁን ላይ አስፈላጊነቱ አጠራጣሪ ያልሆነውን የሀገራዊ ሉዓላዊነቷን የማጠናከር ስራ በትኩረት መሥራት አለባት።
🟠 ያለ ሉዓላዊነት የሀገርን መሠረታዊ ጥቅሞች በማንኛውም ዘርፍ ማስከበር ፈጽሞ የማይቻል ነው።
🟠 ሩሲያ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት፣ በራሳቸው ለሚንቀሳቀሱ ስርዓቶች እና ለዲጂታል መድረኮች ቴክኖሎጂ ልማት ልዩ ትኩረት ትሰጣለች።
🟠 መንግሥት በሀገር በቀል የቴክኖሎጂ መፍትሄዎች ላይ ተመሥርተው ለሚደረጉ የንግድ ዘርፍ ኢንቨስትመንቶች እና ዘመናዊ አሰራሮች ድጋፍ ያደርጋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X