6ኛው የአፍሪካ ወጣት አመራሮች ዲፕሎማሲያዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
ጉባኤው በዋናነት በኅጉሪቱ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ቀጣናዊና የጸጥታና ደህንነት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ ለቀጣዮቹ 5 ቀናት በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን አፍሪካ አዳራሽ የሚካሄድ ነው።
የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)ን ጨምሮ የመንግሥት ባለሥልጣናት ከአኅጉሪቱ የተለያዩ ሀገራት የተወከሉ የወጣት ማኅበራት አመራሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በጉባኤው የመክፈቻ ሥነ-ስርዓት ላይ ተገኝተዋል።
ጉባኤው በሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በኢትዮጵያ ወጣቶች ውይይት ለሰላም ማኅበር (EYDPA) ትበብር የተዘጋጀ መሆኑን የስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠኛ ዘግቧል፡፡
በስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ የተቀረጸ ቪዲዮ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X