የኢራን አብዮታዊ ዘብ በእስራኤል እና በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች 80ኛ ዙር ኢላማቸውን የጠበቁ ሚሳኤሎች ጥቃት ፈጸመ
10:42 25.03.2026 (የተሻሻለ: 10:44 25.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በእስራኤል እና በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች 80ኛ ዙር ኢላማቸውን የጠበቁ ሚሳኤሎች ጥቃት ፈጸመ
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይል ስልታዊ ወታደራዊ እና የሎጂስቲክስ ማዕከላትን ኢላማ ያደረጉ የ"እውነተኛ ቃል ኪዳን 4" ዘመቻ 80ኛ ዙር ጥቃቶችን ፈጽሟል፡፡ በዚህም፦
◻ የሰሜኑን ግንባር እንቅስቃሴ የሚመራው በሳፌድ የሚገኘው የእስራኤል ወታደራዊ ዕዝ ተመትቷል።
◻ ቴል አቪቭ፣ ኪርያት ሽሞና እና ብኔ ብራክ በትክክለኛ ኢላማ መቺ ሚሳኤሎች ተደብድበዋል።
◻ በአሊ አል-ሳሌም፣ አሪፍጃን፣ አል-አዝራቅ እና ሼክ ኢሳ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ኢላማ ተደርገዋል።
◻ በጥቃቱ ወቅት በፈሳሽ እና በጠንካራ ነዳጅ የሚሰሩ ሚሳኤሎች የሆኑት ኸይባር-ሸካን፣ ኢማድ እና ሰጂልን ጨምሮ ከከባድ አውዳሚ ድሮኖች ጋር ጥቅም ላይ ውለዋል።
◻ ዘመቻው በእስራኤል ኃይሎች መሰብሰቢያ ቦታዎች ላይ አስቀድሞ የታወጁ ተከታታይ ጥቃቶች መጀመሪያ መሆኑ ተገልጿል።
◻ አብዮታዊ ዘቡ እንደገለጸው፤ የሚዲያ ሳንሱር የጥቃቱን መጠን አሳንሶ ለማሳየት እየሞከረ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X