ናሚቢያ የኤለን መስክ የስታርሊንክ ሳተላይት የሥራ ፈቃድ እንዳያገኝ አገደች

ሰብስክራይብ

ናሚቢያ የኤለን መስክ የስታርሊንክ ሳተላይት የሥራ ፈቃድ እንዳያገኝ አገደች

የናሚቢያ የኮሙዩኒኬሽን ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ውሳኔውን ያስተላለፈበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፤ በባለሥልጣኑ ተነሳሽነት ወይም በስታርሊንክ ጥያቄ በሚቀጥሉት 90 ቀናት ውስጥ እንደገና ሊታይ እንደሚችል መግለጹን አንድ የደቡብ አፍሪካ የዜና ወኪል ዘግቧል።

እንደ ዘገባው ከሆነ፤ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣኑ በኅዳር ወር 2017 ዓ.ም ስታርሊንክ ያለ ፈቃድ እየሠራ ነው በሚል አገልግሎቱን እንዲያቆም እና ሕገ-ወጥ የተባሉ የኩባንያው መሣሪያዎች እንዲወረሱ መመሪያ ሰጥቶ ነበር።

ስታርሊንክ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ካሜሩን ባሉ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ተመሳሳይ የሕግ መሰናክሎች እና ከመንግሥት የቴሌኮም ተቋማት ተቃውሞ እየገጠመው ይገኛል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0