ዚምባብዌ ምርትን ከሀገር ውስጥ ገበሬዎች መግዛት የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አወጣች

ሰብስክራይብ

ዚምባብዌ ምርትን ከሀገር ውስጥ ገበሬዎች መግዛት የሚያስገድድ አዲስ መመሪያ አወጣች

የግብርና ሚኒስትሩ አንክሺየስ ማስሁካ፤ በአዲሱ መመሪያ መሠረት የዱቄት ፋብሪካዎች፣ የእንስሳት መኖ አምራቾች እና የምግብ ማቀነባበሪያዎች ቢያንስ 40 በመቶ የሚሆነውን ጥሬ ዕቃ ከሀገር ውስጥ ገበሬዎች መግዛት እንደሚኖርባቸው ገልፀዋል።

ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይህ ለውጥ፤ የእህል ገቢ ምርትን ለመቀነስ፣ የሀገር ውስጥ ምርታማነትን ለማሳደግ እና የግብርና የክምችት ሰንሰለትን ለማጠናከር ያለመ ነው።

መመሪያው ለሀገር ውስጥ በቆሎ፣ ስንዴ፣ አኩሪ አተር፣ የሱፍ አበባ እና ጥጥ ቅድሚያ መስጠትን የግዴታ ያደርጋል።

በተጨማሪም የገቢ ምርቶች ዋጋ ከሀገር ውስጥ የማምረቻ ወጪ በታች ሆኖ ከተገኘ፤ የዋጋ ልዩነቱ ወደ ግብርና ተዘዋዋሪ ፈንድ ገቢ ይደረጋል። ይህም ርካሽ የገቢ ምርቶችን ለመገደብ እና የሀገር ውስጥ ገበሬዎችን በገንዘብ ለመደገፍ ታስቦ የተዘጋጀ አሠራር ነው።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0