ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አነስተኛ አምራቾችን ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የሚቀይር አዲስ አሠራር ይፋ አደረገ
18:06 23.03.2026 (የተሻሻለ: 18:41 23.03.2026)

ሰብስክራይብ
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አነስተኛ አምራቾችን ወደ ኢንዱስትሪ መሪነት የሚቀይር አዲስ አሠራር ይፋ አደረገ
የክልሉ የማዕድን ልማት ቢሮ አነስተኛ ወርቅ አምራቾችን በ5 ሄክታር መሬት ላይ በማደራጀት እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ እንዳደረገ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
አደረጃጀቱን በተመለከተ የተጠቀሱ አንኳር ነጥቦች፦
🟠 የአካባቢው ነዋሪዎች የቆየ ልምድና እውቀታቸውን ከሕጋዊ አሠራር ጋር በማቀናጀት ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ ዕድል ፈጥሯል፣
🟠 አምራቾቹን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወደ ተሻለ የኢንዱስትሪ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት እየተሠራበት ነው፣
🟠 ባለሀብቶች ከአነስተኛ አምራቾች ጋር በጋራ እንዲሠሩ ወይም ከ5 እስከ 50 ሄክታር መሬት በመስጠት በኩባንያ ደረጃ እንዲንቀሳቀሱ ሂደቶች እየተመቻቹ ይገኛል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ናስር መሐመድ ይህ ተነሳሽነት “የክልሉን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠንና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ያለመ ነው” ብለዋል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ50 ኩንታል በላይ ወርቅ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉም ተገልጿል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የክልሉ የማዕድን ልማት ቢሮ አነስተኛ ወርቅ አምራቾችን በ5 ሄክታር መሬት ላይ በማደራጀት እስካሁን ከ50 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ እንዳደረገ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
አደረጃጀቱን በተመለከተ የተጠቀሱ አንኳር ነጥቦች፦
🟠 የአካባቢው ነዋሪዎች የቆየ ልምድና እውቀታቸውን ከሕጋዊ አሠራር ጋር በማቀናጀት ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ ዕድል ፈጥሯል፣
🟠 አምራቾቹን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ወደ ተሻለ የኢንዱስትሪ ደረጃ ለማሸጋገር በትኩረት እየተሠራበት ነው፣
🟠 ባለሀብቶች ከአነስተኛ አምራቾች ጋር በጋራ እንዲሠሩ ወይም ከ5 እስከ 50 ሄክታር መሬት በመስጠት በኩባንያ ደረጃ እንዲንቀሳቀሱ ሂደቶች እየተመቻቹ ይገኛል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ናስር መሐመድ ይህ ተነሳሽነት “የክልሉን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠንና ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ያለመ ነው” ብለዋል፡፡
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ሰባት ወራት ከ50 ኩንታል በላይ ወርቅ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገቢ ማድረጉም ተገልጿል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X