የኢራን ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የቅንጦት መኪኖችን መሄጃ አሳጥቶ በላሙ ወደብ አስቀርቷል
16:42 23.03.2026 (የተሻሻለ: 16:44 23.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢራን ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የቅንጦት መኪኖችን መሄጃ አሳጥቶ በላሙ ወደብ አስቀርቷል
ፖርሽ እና ቮልስዋገንን ጨምሮ ከ4 ሺህ በላይ የቅንጦት መኪኖች በሆርሙዝ ወሽመጥ በተፈጠረው መስተጓጎል ምክንያት ከመዳረሻቸው ዱባይ ወደ ኬንያ እንዲዛወሩ ተደርጓል።
መኪኖቹ በላሙ ወደብ መራገፋቸውን እና ሁኔታዎች እስኪረጋጉ ድረስ እዛው እንደሚቆዩ የወደቡ ባለሥልጣናት አረጋግጠዋል። በሚቀጥሉት ቀናት ተጨማሪ 5 ሺህ ተሽከርካሪዎች ወደ ወደቡ ይደረሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የኬንያ ባለሥልጣናት ወደቡ እየጨመረ የመጣውን የተሽከርካሪ ብዛት ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ቢገልጹም፤ የቅንጦት መኪኖቹን እጣ ፈንታ በተመለከት ግን እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X