የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሸከርካሪዎች እንዲወረሱ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ

ኮንትሮባንድ
ኮንትሮባንድ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.03.2026
ሰብስክራይብ
የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሸከርካሪዎች እንዲወረሱ የሚደነግግ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ

ቀደም ሲል በነበረው አዋጅ (ቁጥር 1160/2011) የኮንትሮባንድ ዕቃ የጫኑ ተሸከርካሪዎች ባለቤቶች በወንጀሉ ተካፋይ ካልሆኑ 100 ሺህ ብር ቅጣት ብቻ ከፍለው ንብረታቸውን ይረከቡ እንደነበር የሀገር ውስጥ ሚዲያ በዘገባው አመልክቷል፡፡

ሆኖም ይህ አሠራር ኮንትሮባንድን ለመከላከል በቂ ሆኖ ባለመገኘቱ ማሻሻያው አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱ ተጠቁሟል፡፡ ለዚህም የኮንትሮባንድ ነጋዴው ቅጣቱን ለመክፈል በመስማማት ወንጀሉን መሥራት እንደሚቀጥል መረጃዎች ማሳየታቸውን ዘገባው ጨምሮ ገልጿል፡፡

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከልና በዘርፉ የሚታዩ ክፍተቶችን ለመሙላት ያለመ ነው ተብሏል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0