ኢራን ለሩሲያ ዲፕሎማሲያዊ እና ሰብዓዊ ድጋፍ ምስጋና አቀረበች
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከኢራኑ አቻቸው አባስ አራግቺ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
የውይይቱ አንኳር ነጥቦች፦
◻ ሁለቱ ወገኖች በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በፍጥነት እየተካረረ ስለመጣው ሁኔታ የተወያዩ ሲሆን ለውጥረቱ መባባስ የአሜሪካ እና የእስራኤል እርምጃዎች ምክንያት እንደሆኑ አንስተዋል።
◻ ላቭሮቭ የቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫን ጨምሮ በኢራን የኒውክሌር መሠረተ ልማቶች ላይ የተሰነዘረው ጥቃት የሩሲያ ሠራተኞች ላይ የሚፈጥረውን አደጋ እና በአጠቃላይ በቀጣናው ሊያስከትል የሚችለውን የአካባቢ ጥፋት በመጥቀስ አጥብቀው አውግዘዋል።
◻ ሩሲያ እና ኢራን ግጭቱ ወደ ካስፒያን ባሕር ሊስፋፋ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
◻ ሞስኮ በአፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ እና የሁሉንም ወገኖች በተለይም የኢራንን ጥቅም ግምት ውስጥ ያስገባ የፖለቲካ መፍትሄ እንዲበጅ ጥሪ አቅርባለች።
◻ ሩሲያ ይህንን አቋሟን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንደምታራምድ በድጋሚ አረጋግጣለች።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ከኢራኑ አቻቸው አባስ አራግቺ ጋር በስልክ ተወያይተዋል።
የውይይቱ አንኳር ነጥቦች፦
◻ ሁለቱ ወገኖች በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በፍጥነት እየተካረረ ስለመጣው ሁኔታ የተወያዩ ሲሆን ለውጥረቱ መባባስ የአሜሪካ እና የእስራኤል እርምጃዎች ምክንያት እንደሆኑ አንስተዋል።
◻ ላቭሮቭ የቡሸር የኒውክሌር ኃይል ማመንጫን ጨምሮ በኢራን የኒውክሌር መሠረተ ልማቶች ላይ የተሰነዘረው ጥቃት የሩሲያ ሠራተኞች ላይ የሚፈጥረውን አደጋ እና በአጠቃላይ በቀጣናው ሊያስከትል የሚችለውን የአካባቢ ጥፋት በመጥቀስ አጥብቀው አውግዘዋል።
◻ ሩሲያ እና ኢራን ግጭቱ ወደ ካስፒያን ባሕር ሊስፋፋ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
◻ ሞስኮ በአፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ እና የሁሉንም ወገኖች በተለይም የኢራንን ጥቅም ግምት ውስጥ ያስገባ የፖለቲካ መፍትሄ እንዲበጅ ጥሪ አቅርባለች።
◻ ሩሲያ ይህንን አቋሟን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንደምታራምድ በድጋሚ አረጋግጣለች።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
