አሜሪካ በኢራን የኃይል ተቋማት ላይ ጥቃት ከሰነዘረች የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን ሙሉ በሙሉ እንዘጋለን - የኢራን አብዮታዊ ዘብ
19:44 22.03.2026 (የተሻሻለ: 19:54 22.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ በኢራን የኃይል ተቋማት ላይ ጥቃት ከሰነዘረች የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን ሙሉ በሙሉ እንዘጋለን - የኢራን አብዮታዊ ዘብ
የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ በኢራን ቁጥጥር ስርና ለጠላት ትራፊክ ብቻ የተዘጋ ይሆናል። አሜሪካ በኢራን የኃይል ማመንጫዎች ላይ ጥቃት ካደረሰች ግን አፋጣኝ የመቀጣጫ እርምጃ ይወሰዳል ሲል ዘቡ ባወጣው መግለጫ አስጠንቅቋል።
▪የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ የወደሙ የኢራን የኃይል ማመንጫዎች ተገንብተው ሥራ እስኪጀምሩ ድረስ ሙሉ በሙሉ ዝግ ሆኖ ይቆያል።
▪ ሁሉም የእስራኤል የኃይል ማመንጫዎች፣ የኢነርጂ መሠረተ ልማቶች እንዲሁም የመረጃና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች የመጠነ ሰፊ ጥቃት ኢላማ ይሆናሉ።
▪ በክልሉ የሚገኙ የአሜሪካ ኩባንያዎች ሙሉ በሙሉ ይወድማሉ።
▪ የአሜሪካ የጦር ሠፈሮች የሚገኙባቸው የጎረቤት ሀገራት የኃይል ማመንጫዎች የኢራን ሕጋዊ የጥቃት ኢላማ ናቸው።
ቪዲዮው በኢራን "እውነተኛ ቃል ኪዳን 4" ኦፕሬሽን 74ኛውን ዙር የሚሳኤል ጥቃት ያሳያል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X