ማኅበረ ቅዱሳን ያዘጋጀው ልዩ የበገና ምሽት መርኃ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሄደ

ሰብስክራይብ

ማኅበረ ቅዱሳን ያዘጋጀው ልዩ የበገና ምሽት መርኃ-ግብር በአዲስ አበባ ተካሄደ

በዝግጀቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ተወካዮች፣ የግብጽ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ተወካይ፣ የኃይማኖት ሰዎች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ተወካዮች መታደማቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።

🪉 ለአስርት ዓመታት በዘለቀው የበገና ዝማሬ አገልግሎታቸው የሚታወቁት መጋቤ ስብኃት አለሙ አጋ መንፈሳዊ ሥራዎቻቸውን አቅርበዋል።

የመርኃ-ግብሩ ዓላማ “በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ዋነኛ ከሚባሉት መንፈሳዊ የምሥጋና እና የጸሎት መሳሪያዎች አንዱ የሆነውን በገናን ጠብቆ ለመጪው ትውልድ ማስተላለፍ ነው” ሲሉ የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ አቶ ካሳሁን ኃይለማርያም ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0