አልጄሪያ የዚንክ እና ሊድ ማዕድን ቁፋሮ ሥራ ጀመረች
16:59 22.03.2026 (የተሻሻለ: 17:04 22.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አልጄሪያ የዚንክ እና ሊድ ማዕድን ቁፋሮ ሥራ ጀመረች
በአልጄሪያ ሰሜን ምስራቅ ቤጃያ በተባለ አካባቢ የሚገኘውና በዓለማችን ካሉ እጅግ የበለፀጉ የማዕድን ክምችቶች አንዱ የሆነው ይህ የማዕድን ስፍራ፤ የሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪን ለማጠናከር እና አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የፕሮጀክቱ ቁልፍ መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
የታቀደ ዓመታዊ ምርት፦ 170 ሺህ ቶን ዚንክ እና 30 ሺህ ቶን ሊድ፣
የተገመተ የማዕድን ክምችት፦ 34 ሚሊዮን ቶን ያልተጣራ ማዕድን፣
የሚጠበቅ ዓመታዊ ገቢ፦ ወደ 215 ሚሊዮን ዶላር ገደማ።
ይህ ፕሮጀክት ለእነዚህ ማዕድናት ያለውን የሀገር ውስጥ ፍላጎት ከማሟላቱም በላይ ምርቱን ወደ ውጭ ሀገር ለመላክ መንገድ ይከፍታል ተብሏል።
ቪዲዮው የአልጄሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሲፊ ግሪብ ረቡዕ ዕለት ፕሮጀክቱን ሲያስመርቁ ያሳያል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X