የኢትዮጵያ ደኖች የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወቱ ነው ተባለ
15:43 22.03.2026 (የተሻሻለ: 16:44 22.03.2026)

ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ደኖች የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወቱ ነው ተባለ
“የሀገሪቱ ደኖች 2.7 ቢሊዮን ቶን የካርበን ክምችት በመያዝ ዓለምን ከብክለት እየታደጉ ነው” ሲሉ የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳይሬክተር ከበደ ይማም ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ይህ የካርበን መጠን ባይኖር ወይም ደኖቹ ቢወድሙ፤ ወደ 10 ቢሊዮን ቶን የሚጠጋ የካርበን ዳይኦክሳይድ ጋዝ በቀጥታ ወደ አየር ሊለቀቅ እንደሚችልና የአየር ንብረት ብክለትን በከፍተኛው ያባብስ እንደነበር ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ የደን ልማት ሀገራዊ ፋይዳንም አንስተዋል፦
ለሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ከፍተኛ የሚባል ድርሻ አለው፣
ከ28-47% የሚሆነው የኅብረተሰብ ክፍል ከደን ሀብት ቀጥተኛ ገቢ ያገኛል፡፡
ኢትዮጵያ የካርበን ክምችቷን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ገቢ ለማግኘት እየሠራች እንደሆነም ተጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
“የሀገሪቱ ደኖች 2.7 ቢሊዮን ቶን የካርበን ክምችት በመያዝ ዓለምን ከብክለት እየታደጉ ነው” ሲሉ የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳይሬክተር ከበደ ይማም ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ይህ የካርበን መጠን ባይኖር ወይም ደኖቹ ቢወድሙ፤ ወደ 10 ቢሊዮን ቶን የሚጠጋ የካርበን ዳይኦክሳይድ ጋዝ በቀጥታ ወደ አየር ሊለቀቅ እንደሚችልና የአየር ንብረት ብክለትን በከፍተኛው ያባብስ እንደነበር ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሩ የደን ልማት ሀገራዊ ፋይዳንም አንስተዋል፦
ለሀገሪቱ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት ከፍተኛ የሚባል ድርሻ አለው፣
ከ28-47% የሚሆነው የኅብረተሰብ ክፍል ከደን ሀብት ቀጥተኛ ገቢ ያገኛል፡፡
ኢትዮጵያ የካርበን ክምችቷን ለዓለም ገበያ በማቅረብ ገቢ ለማግኘት እየሠራች እንደሆነም ተጠቁሟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X