የከተማ አውቶቡሶች ሞተራችውን በመቀየር የተፈጥሮ ጋዝ መጠቀም ሊጀምሩ እንደሆነ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ

የከተማ አውቶቡሶች
የከተማ አውቶቡሶች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.03.2026
ሰብስክራይብ
የከተማ አውቶቡሶች ሞተራችውን በመቀየር የተፈጥሮ ጋዝ መጠቀም ሊጀምሩ እንደሆነ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታወቀ

በቅርቡ በቃሊቲ፣ በአዳማ እና በድሬዳዋ የጋዝ ማደያዎች ሥራ እንደሚጀምሩ የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ደስታው መኮንን ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልጸዋል፡፡

ኃላፊው ከሦስት ዓመት ተኩል በኋላ የሚጠናቀቀው የሀገር ውስጥ የነዳጅ ማጣሪያ ግንባታ 80 በመቶ የሚሆነውን የሀገር ውስጥ ፍላጎት እንደሚሸፍንም ጠቁመዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዓመት 111 ሚሊዮን ሊትር ፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ያመርታል የተባለውን የካሉብ ፕሮጀክት ማስጀመሯ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም ነዳጅ የሚጠቀሙ ከባድ መኪኖች ወደ ሀገር እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0