የኬንያ ፖሊስ በተለያዩ የሀገሪቱ አውራጃዎች ሰላም የማስፈን ዘመቻ ጀመረ

የኬንያ ፖሊስ
የኬንያ ፖሊስ  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.03.2026
ሰብስክራይብ
የኬንያ ፖሊስ በተለያዩ የሀገሪቱ አውራጃዎች ሰላም የማስፈን ዘመቻ ጀመረ

የብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት በኬንያ ሰሜናዊ ክፍሎች የሚታየውን ሽፍተኝነት ለመግታት፣ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያዎችን ለመሰብሰብ እና እየተባባሰ የመጣውን የከብት ዘረፋ ለመከላከል፤ የተለያዩ የደህንነት አካላትን ያሳተፈ የጋራ ዘመቻ መጀመሩን በይፋዊ መግለጫው አስታውቋል።

ዘመቻው ጥቃት ሊፈጸምባቸው ይችላል ተብለው የተለዩ ቦታዎችን ኢላማ ያደረገ ሲሆን በከፍተኛ የደህንነት ኃይል፣ በአየር ቅኝት እና የአየር ድጋፍ የታገዘ ነው።

በሰሜን ኬንያ በሚገኙ ተቀናቃኝ የአርብቶ አደር ማኅበረሰቦች መካከል ግጭቶች የተለመደ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ካለፉት ጊዜያት በተለየ እየከፋ መምጣቱ ተነግሯል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0