የግብርና ሚኒስቴር በ2.32 ቢሊየን ብር የወጣባቸው የግብርና መሳሪያዎችን ለክልሎች እንዳከፋፈለ አስታወቀ

ግብርና ሚኒስቴር
ግብርና ሚኒስቴር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.03.2026
ሰብስክራይብ
የግብርና ሚኒስቴር 2.32 ቢሊየን ብር የወጣባቸው የግብርና መሳሪያዎችን ለክልሎች እንዳከፋፈለ አስታወቀ


“ድጋፉ ግብርናን ለማዘመን፣ ምርታማነትን ለማሳደግና የምርት ጥራትን በማስጠበቅ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚደረገው ሀገራዊ ጥረት አካል ነው” ሲሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ተናግረዋል፡፡


ለክልሎች የተሠራጩት የሜካናይዜሽን መሳሪያዎች፦

63 ትራክተሮች፣
71 ወኪንግ ትራክተሮች፣
150 የሩዝ ማቀነባበሪያ ማሽኖች፣
4 ባለብዙ ደረጃ እንቁላል መታቀፊያዎች፣
460 በፀሃይ ኃይል የሚሠሩ የውሃ መሳቢያ ፓምፖች፣
5 የከርሰ ምድር ውሃ ማውጫ ማሽኖ፡፡

በተጨማሪም የዘርፉን አሠራር ለማሳለጥ የሚረዱ 15 የመስክ መገልገያ ተሽከርካሪዎች፣ 243 ሞተር ሳይክሎች እና 980 ዴስክቶፕና ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች አብረው መሰጠታቸው ተዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0