በናታንዝ የኒውክሌር ተቋም ላይ የተፈጸመው ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ የጣሰ ነው - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

ናታንዝ የኒውክሌር ተቋም
ናታንዝ የኒውክሌር ተቋም - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.03.2026
ሰብስክራይብ
በናታንዝ የኒውክሌር ተቋም ላይ የተፈጸመው ጥቃት ዓለም አቀፍ ሕግን በግልጽ የጣሰ ነው - የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ

እስራኤል እና አሜሪካ በናታንዝ የዩራኒየም ማበልጸጊያ ተቋም ላይ ጥቃት እንደፈጸሙ እና ምንም ዓይነት የጨረር መፍሰስ አለማጋጠሙን የኢራን የአቶሚክ ኢነርጂ ድርጅት ቀደም ሲል ማስታወቁ ይታወሳል።

አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ወታደራዊ፣ ሲቪል እና ከሁሉም በላይ ደግሞ "አደገኛ በሆኑ የኒውክሌር ተቋማት ላይ የሰላማዊ ሰዎችን ሕይወት፣ የጨረር ወይም አካባቢያዊ አደጋን ችላ በማለት መጠነ ሰፊ ጥቃቶችን እየሰነዘሩ ይገኛሉ” ሲሉ ማሪያ ዛካሮቫ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን የዩራኒየም ማበልጸጊያ ተቋም ላይ የፈጸሙትን ጥቃት በገለልተኝነት ሊገመግሙ ይገባል ሲሉም አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0