ግብፅ የምስራቅ ናይል የነጠላ ሐዲድ ባቡር በይፋ ሥራ አስጀመረች - የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት
11:48 21.03.2026 (የተሻሻለ: 12:04 21.03.2026)
ሰብስክራይብ
ግብፅ የምስራቅ ናይል የነጠላ ሐዲድ ባቡር በይፋ ሥራ አስጀመረች - የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት
እ.ኤ.አ በ2019 ግንባታው የተጀመረው የካይሮ ፈጣን ሞኖሬይል በአፍሪካ ረጅሙ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ሞኖሬሉ ሁለት መስመሮችን ያቀፈ ይሆናል፡-
ምስራቅ ናይል፦ መዲናት ናስርን (የምስራቅ ካይሮ አካባቢ) ከአዲሱ የአስተዳደር ዋና ከተማ ጋር ያገናኛል፣
ምዕራብ ናይል፦ ጊዛን ከሲክስ ኦፍ ኦክቶበር ከተማ (የምዕራብ ሰፈር) ጋር ያገናኛል።
▫የምዕራብ ናይል ግንባታ በስድስት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የግብፅ የትራንስፖርት ሚኒስትር ካሜል አል-ዋዚር ተናግረዋል።
▫መስመሩ 100 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን 35 ጣቢያዎችን ያገለግላል።
▫ባቡሮቹ በሰዓት 80 ኪ.ሜ የመጓዝና በቀን 1 ሚሊዮን ተሳፋሪዎች የመያዝ አቅም ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።
የግብፅ ባለሥልጣናት የነጠላ ሐዲድ ባቡሩ በታላቋ ካይሮ ያለውን መጨናነቅ ለማቃለል ቁልፍ ተነሳሽነት ነው ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X