ግብፅ የምስራቅ ናይል የነጠላ ሐዲድ ባቡር በይፋ ሥራ አስጀመረች - የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት

ሰብስክራይብ

ግብፅ የምስራቅ ናይል የነጠላ ሐዲድ ባቡር በይፋ ሥራ አስጀመረች - የፕሬዚዳንቱ ጽሕፈት ቤት

እ.ኤ.አ በ2019 ግንባታው የተጀመረው የካይሮ ፈጣን ሞኖሬይል በአፍሪካ ረጅሙ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ሞኖሬሉ ሁለት መስመሮችን ያቀፈ ይሆናል፡-

ምስራቅ ናይል፦ መዲናት ናስርን (የምስራቅ ካይሮ አካባቢ) ከአዲሱ የአስተዳደር ዋና ከተማ ጋር ያገናኛል፣

ምዕራብ ናይል፦ ጊዛን ከሲክስ ኦፍ ኦክቶበር ከተማ (የምዕራብ ሰፈር) ጋር ያገናኛል።

▫የምዕራብ ናይል ግንባታ በስድስት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የግብፅ የትራንስፖርት ሚኒስትር ካሜል አል-ዋዚር ተናግረዋል።

▫መስመሩ 100 ኪ.ሜ የሚሸፍን ሲሆን 35 ጣቢያዎችን ያገለግላል።

▫ባቡሮቹ በሰዓት 80 ኪ.ሜ የመጓዝና በቀን 1 ሚሊዮን ተሳፋሪዎች የመያዝ አቅም ይኖራቸዋል ተብሎ ይጠበቃል።

የግብፅ ባለሥልጣናት የነጠላ ሐዲድ ባቡሩ በታላቋ ካይሮ ያለውን መጨናነቅ ለማቃለል ቁልፍ ተነሳሽነት ነው ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0