ኢራን ከ15 ዓመታት በፊት ከተተራመሰችው ሊቢያ ጋር ተመሳሳይነት እንዳላት የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ገለጹ
18:50 20.03.2026 (የተሻሻለ: 18:54 20.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢራን ከ15 ዓመታት በፊት ከተተራመሰችው ሊቢያ ጋር ተመሳሳይነት እንዳላት የፖለቲካ ሳይንቲስቱ ገለጹ
አብደልሀቅ ናጂብ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት፣ ሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ የጋዝ እና የነዳጅ አምራቾች ሲሆኑ፣ እ.ኤ.አ. በ2011 ኔቶ በሊቢያ ጣልቃ እንዲገባ ካደረጉት ዋና ዋና ምክንያቶች አንዱ ነዳጅ ነበር።
ናጂብ አክለውም፣ “ የሊቢያ ነዳጅ እርግማን ነው የሆነባት። ሊቢያን ለመውረር እና ለማፈራረስ ዋነኛው ምክንያት ነዳጅ ነበር። ኔቶ ጣልቃ የገባው ለሰብአዊ መብት፣ ለዲሞክራሲ ወይም ለሌላ ሳይሆን ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም ብቻ ነበር” ብለዋል።
በሊቢያ የተካሄደው ጦርነት “የጥፋት ሳጥንን የከፈተ” ሲሆን፣ በተለይም በሳህል ቀጣና ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ አሸባሪዎች የመስፋፋት መንገድ መክፈቱን ባለሙያው አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ. በጥቅምት 2011 በነበረ አንድ ቃለ መጠይቅ ላይ፣ የወቅቱ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሂላሪ ክሊንተን ስለ ሙአመር ጋዳፊ ሞት ሲናገሩ፤ “መጣን፣ አየን፣ እሱም ሞተ” ማለታቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X