በጎርጎሮሳዊያኑ 2011 የነበረውን የኔቶ ጣልቃ ገብነትን ተከትሎ ሊቢያ ተከፋፍላለች - የኒጀር የፖለቲካ ሳይንቲስት

ሰብስክራይብ

በጎርጎሮሳዊያኑ 2011 የነበረውን የኔቶ ጣልቃ ገብነትን ተከትሎ ሊቢያ ተከፋፍላለች - የኒጀር የፖለቲካ ሳይንቲስት

​በሊቢያ በተቀሰቀሰው ትርምስ ምክንያት የሳህል ሀገራት ደህንነት መጎዳቱን ኢሱፉ ቡባካር ካዶ ማጋጊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

ባለሙያው ሲያብራሩም፣ "ይህ ጣልቃ ገብነት ሊቢያን በታትኗታል። ይህም በአፍሪካ አኅጉር ላይ የራሱ የሆኑ መዘዞች ነበሩት። በሊቢያ የነበሩ ግዙፍ የጦር መሳሪያ ግምጃ ቤቶች እንዲከፈቱ ተደርገው፤ አሸባሪዎች፣ የታጠቁ ወንበዴዎች እና የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪዎች እነዚህን መሳሪያዎች ወደ ሳህል ቀጣና እንዲያፈሱ ተደርጓል" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

አክለውም፣ የኔቶ ዓላማ ሙአመር ጋዳፊን ከስልጣን ማውረድ ብቻ ሳይሆን "የሊቢያን ሀብት በእጁ ለማስገባት እና ሊቢያ የአኅጉሪቱን የኢኮኖሚ ውህደት ለማፋጠን የምታደርገውን ጥረት ለማደናቀፍ ነው" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0