ኢትዮጵያ የተጣራ የውጭ ሀብት ጉድለቷን በአንድ ዓመት ውስጥ በሁለት ሦስተኛ ቀነሰች

ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የተጣራ የውጭ ሀብት ጉድለቷን በአንድ ዓመት ውስጥ በሁለት ሦስተኛ ቀነሰች

​በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም አዲስ የወጣው የሩብ ዓመት የኢኮኖሚ መገለጫ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ የኢትዮጵያ የተጣራ የውጭ ሀብት ጉድለት እ.ኤ.አ. በነሐሴ 2024 ከነበረበት 498.9 ቢሊዮን ብር፣ በነሐሴ 2025 ወደ 164.7 ቢሊዮን ብር ዝቅ ብሏል።

​ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ እ.ኤ.አ. በሰኔ 2024 ጉድለቱ 245.3 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን፣ ይህም ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ የሀገሪቱ የውጭ የፋይናንስ አቅም ቀጣይነት ያለው መሻሻል ማሳየቱን ይጠቁማል።

ይህ ለውጥ የተገኘው ከወጪ ንግድ፣ ከውጭ ሀገር ከሚላክ ገንዘብ እና ከመደበኛ የፋይናንስ ድጋፎች በተገኘው ጠንካራ ገቢ ምክንያት የውጭ ሀብት ክምችቱ ከእዳው አንጻር በፍጥነት በማደጉ ነው።

ጠቅላላ ዓለም አቀፍ መጠባበቂያ ክምችት በጎርጎሮሳውያኑ መስከረም 2024 ከነበረበት 3.3 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2026 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ወደ 5.5 ቢሊዮን ዶላር ማደጉ ተዘግቧል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0