


ፕሬዝዳንት ትራምፕ የወታደራዊ ዘመቻው ዓላማ የኢራን አገዛዝ የሚደቅነውን "ስጋት" ማስወገድ መሆኑን ገልጸዋል።
በጄኔቫ የተካሄደው የመጨረሻው የኢራን እና የአሜሪካ ንግግር የካቲት19 ቀን (እ.ኤ.አ) ያለ ስምምነት በመጠናቀቁ፣ ከጥቂት ቀናትበኋላ ዲፕሎማሲው በጦርነት ተተክቷል።
በካቲት 28 ቀን 2026 (እ.ኤ.አ) አምስት የኢራን ከተሞች በቦምብ ፍንዳታ ተናውጠዋል፦ እነርሱም ቴህራን፣ ኢስፋሃን፣ ቁም፣ ካራጅ እና ኬርማንሻህ ናቸው። የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላ አሊ ካሜኒ መኖሪያ ቤት በቀጥታ በተሰነዘረ ጥቃት ሙሉ በሙሉወድሟል።
እስራኤል ቀድሞ የመምታት ጥቃት ፈጽማለች። የጥቃቱ ኢላማዎችበፎርዶው፣ ናታንዝእና ኢስፋሃን የሚገኙ የኒውክሌር ተቋማት እንዲሁም የኢራን አብዮታዊ ዘብ(IRGC) ዋና መሥሪያቤቶች፣ የአየር መከላከያ ጣቢያዎች እና የወታደራዊ-ኢንዱስትሪው ስብስብ ማዕከላት ናቸው። እስራኤል ወታደራዊ ዘመቻዋን "ላየንስ ሮር" ስትል ሰይማዋለች። ሚሳኤሎቹ ወታደራዊ ኢላማዎችን ብቻ ሳይሆን የሲቪል መሠረተ ልማቶችንም መምታታቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል።



ዒላማዎቹ የሚከተሉትን ያካትታሉ፦ |
በሃይፋ የሚገኘው የእስራኤል የባህር ኃይል እና የራማት ዳዊት የአየር ኃይል ጣቢያ፤ |
በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ 5ኛ የባህር ኃይል ክፍለ ጦር ዋና መሥሪያ ቤት፤ |
በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የሚገኘው የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ ልማት እና የጄበል አሊ ወደብ (በጥቃቱ ምክንያት እሳት ተቀስቅሷል)፤ |
በኩዌት የሚገኙ ተቋማት(በዚህ ጥቃት ሦስት የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል።) |





መላምቶች እና ምርመራ፦ |
l ኢራን አሜሪካን እና እስራኤልን በጦር ወንጀል ከሰሰች፤ መጋቢት 6 ቀን (እ.ኤ.አ) የሰነዘረችው የአጸፋ ጥቃትም "ለሚናብ ሕፃናት የተወሰደ በቀል" እንደሆነ ገልጻለች። |
l መጀመሪያ ላይ አሜሪካ እጇ እንዳለበት ብታስተባብልም፣ ትራምፕ ግን ጥቃቱ በራሱ በኢራን የተፈጸመ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመው ነበር። ሆኖም የፔንታጎን የውስጥ ምርመራ ጥቃቱ በአሜሪካ ጦር የመፈጸም ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን አመልክቷል። |
l የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት ከሆነ፣ አሜሪካ እና እስራኤል በደቡብ ኢራን በሚገኝ የሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ጥቃት የፈጸሙት በስለላ ስህተት ወይም በሰውሰራሽ አስተውሎት አልጎሪዝም ብልሽት ምክንያት ተቋሙን እንደ ወታደራዊ ኢላማ በስህተት በመመደባቸው ሊሆን ይችላል። |



በአገሪቱ የ40 ቀናት የሐዘን አዋጅ ታውጇል። በአሜሪካ እና እስራኤ ልጥቃት የአያቶላው ልጅ፣ አማች፣የልጅ ልጅእና ምራትም አብረው ተገድለዋል።
የሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት ሞትም ተረጋግጧል፦የመከላከያ ሚኒስትር አዚዝ ናሲርዛዴህ፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) አዛዥ መሐመድ ፓክፑር፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም አብዱልረሂም ሙሳቪ እና አማካሪው አሊሻምካኒ ይገኙበታል።
አያቶላ አሊ ሬዛ አራፊ በጊዜያዊነት የአገሪቱ ጠቅላይ መሪ ሆነው ተሹመዋል።

መጋቢት 2 ቀን 2026 (እ.ኤ.አ) ኢራን በእስራኤል፣ በቀጠናው በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና በኢራቅ በሚገኘው የኢርቢል አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ተከታታይ ጥቃቶችን ሰንዝራለች። በዱባይ፣ ዶሃ እና ባህሬንምየፍንዳታ ድምፆች ተሰምተዋል። የኢራን አብዮታዊ ዘብ ከ700 በላይ ድሮኖችን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችን በመጠቀም60 ስልታዊ እና 500 ወታደራዊ የአሜሪካ እና የእስራኤል ተቋማት ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
• ከመጋቢት 3 እስከ መጋቢት 10 ቀን (እ.ኤ.አ) ባለው ጊዜ ውስጥ የኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) በባህሬን የሚገኘውን የአሜሪካ አየር ኃይል ጣቢያ በሚሳኤል እና በድሮን ደብድቧል። በተጨማሪም በእስራኤል የሚገኙ ኢላማዎችን፦ በቂሳሪያ የሚገኘውን የጦር ሰፈር፣ በብኒብራክ፣ ፔታህቲክቫ፣ ምዕራባዊ ጋሊሊ፣ ቤንጉሪዮን አውሮፕላን ማረፊያ እና በቴልአቪቭ የሚገኘውን የመከላከያ ሚኒስቴር መትቷል።
• የኢራን አብዮታዊ ዘብ ጥቃቱን ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገሩን እና ስልታዊ እንዲሁም ድምፅን ከአምስት እጥፍ በላይ የሚቀድሙ (ሃይፐርሶኒክ ) ሚሳኤሎችን (ጋድር፣ ኢማድ፣ፋታህ እናኬይባር ሸካን) እየተጠቀመ መሆኑን አስታውቋል። የአየር እና የጠፈር ኃይሎች ዕዝ ከእንግዲህ በኋላ የሚሳኤሎቹ አረር ቢያንስ አንድቶን እንደሚመዝን ገልጸዋል። ኢራን በእስራኤል ላይ እጅግ ዘመናዊ የሆነውን "ኮራምሻህር-4" (2,000 ኪ.ሜየሚጓዝ እና 1,500 ኪ.ግ አረር መሸከም የሚችል) ሚሳኤል ተጠቅማለች።
• ኢራን 22ኛውን የ"ኮራምሻህር-4" እና የ"ፋታህ" ሚሳኤል ጥቃት ማዕበል ሰንዝራለች። አብዮታዊ ዘቡ በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና በጆርዳን የሚገኙየ"ታድ" (THAAD) ሚሳኤል መከላከያ ራዳሮችን፣ እንዲሁም በኳታር የሚገኘውን "ኤፍፒኤስ132" የተሰኘ ራዳርማውደሙን ይፋ አድርጓል።

የኢራኑ ፕሬዝዳንት በበኩላቸው ጎረቤት አገራት ከግዛታቸው የሚነሱ ጥቃቶች ከሌሉ ወይም በኢራን ላይ እንዲፈጸም ካልፈቀዱ፣ ኢራንም በእነርሱ ላይ የምታደርገውን ጥቃት እንደምታቆም ገልጸዋል።
l ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለሚደረግና ከ10 ዓመታት በላይ ለሚዘልቅ ጦርነት ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች፦ "ከእንግዲህ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ሊታሰብ የማይችል ጉዳይ ነው" ብላለች።
የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ሜሎኒ፦ በሮም ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የፈጸሙትን ጥቃት አውግዘዋል። በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ ዘመቻ "ከዓለም አቀፍ ሕግ ውጭ የሆኑ የአንድ ወገን ጣልቃ ገብነቶች" አካል መሆኑን ገልጸዋል።

ኢራን በይፋ በሰጠችው መግለጫ በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያላትን የባህር ላይ ሉዓላዊነት እንደምታስከብር ገልጻለች። ኢራን የሚያልፉ መርከቦችን በዓለም አቀፍ ፕሮቶኮል መሠረት እንደምታስተናግድ ብትገልጽም፣ "ለወታደራዊ ዓላማ በሌሎች አገራት የሚያገለግሉ" የንግድ መርከቦችን ግን ለይታ እንደምታውቅና "እንዲንቀሳቀሱ እንደማትፈቅድ" አስታውቃለች።
ኢራን ቆየት ብላ ባወጣችው መግለጫ፣ ማንኛውም የአረብ ወይም የአውሮፓ አገር የእስራኤልን እና የአሜሪካን አምባሳደሮች ከግዛቱ ካስወጣ፣ በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል በነፃነት የመንቀሳቀስ መብት እንደሚሰጠው ገልጻለች።

• እስከ መጋቢት18 ቀን 2026 (እ.ኤ.አ)ድረስ በነበረው ግጭት ከፍተኛ የሰው ሕይወት መጥፋት እና ሰፊ ሰብአዊ ቀውስ ተከስቷል።
• እንደ ኢራን መንግሥት ይፋዊመረጃ ቢያንስ 1,348 ሲቪሎች ሲገደሉ፣ከ17,000 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቆስለዋል።
• በጎረቤት አገራት፦ግጭቱ ጎረቤት አገራትንም ነክቷል። በእስራኤል አራት ሕፃናትን ጨምሮ 12 ሰዎች ተገድለዋል። በሊባኖስ 98 ሕፃናት እና 52 ሴቶችን ጨምሮ ቢያንስ 687 ሰዎች እና ሦስት ወታደሮች ተገድለዋል። በባሕረ ሰላጤዉ አገራት ሰባት የአሜሪካ ወታደሮችን ጨምሮ 24 ሰዎች ሲገደሉ፣ በኢራቅ ደግሞ 31 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
• በቀጠናው በቀጥታ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ2,000 በላይ ሆኗል። ሆኖም በኢራን ውስጥ ያለው ሰብአዊ ቀውስ እጅግ የከፋ ነው፤ እንደ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከፍተኛ የስደተኞች ኮሚሽን መረጃ ከሆነ፣ እስከ3.2 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለው ለአገርውስጥ ስደት ተጋልጠዋል።
የኢራን ከፍተኛ የብሔራዊ ደህንነትምክር ቤት ጸሐፊ አሊ ላሪጃኒ መገደል (መጋቢት 17 ቀን ፣ እ.ኤ.አ) በአገሪቱ አመራር ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደማያደርስ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ አስታውቀዋል።

"አሜሪካውያን እና እስራኤላውያን ይህንን እስካሁን ለምን እንዳልተረዱ አላውቅም፤ የኢራን ኢስላማዊ ሪፐብሊክ የጸና የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ተቋማት መዋቅር ያላት አገር ናት" ብለዋል። አራግቺ አክለውም የካቲት 28 (እ.ኤ.አ) ቀን የጠቅላይ መሪው አሊ ካሜኒ ግድያ ከተፈጸመ በኋላም የመንግሥት ሥርዓቱ ሳይናወጥ ሥራውን መቀጠሉን አስታውሰዋል።
መጋቢት 12 ቀን (እ.ኤ.አ) በለንደን የንግድ ልውውጥ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ100 ዶላር በላይ ሆኗል። ይህም ከ2024 ክረምት ወዲህ የተመዘገ በከፍተኛው ዋጋ ነው። ለዚህም ምክንያት የሆነው በባሕረ ሰላጤው ሀገራት ውስጥ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ሲሆን፣ በኢራቅ ጠረፍ አቅራቢያ በነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ የተፈጸመው ጥቃት የኢራቅ ወደቦች ለጊዜው እንዲዘጉና በኦማን የሚገኝ የነዳጅ ማከማቻ እንዲለቀቅ አድርጓል።

ገበያው በሆርሙዝ ሰርጥ በኩል ካለው የነዳጅ አቅርቦት መስተጓጎል ስጋት የተነሳ ከፍተኛ መዋዠቅ እያሳየ ይገኛል።