በሊቢያ የአሜሪካ ጣልቃገብነት ደቡባዊው ዓለም በኔቶ ላይ እምነት እንዲያጣ ሊያደርገው ይገባል

በሊቢያ የአሜሪካ ጣልቃ ገብነት
በሊቢያ የአሜሪካ ጣልቃ ገብነት  - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.03.2026
ሰብስክራይብ
በሊቢያ የአሜሪካ ጣልቃገብነት ደቡባዊው ዓለም በኔቶ ላይ እምነት እንዲያጣ ሊያደርገው ይገባል


​የደቡባዊ ዓለም ሀገራት በሊቢያ ከደረሰው መራር ተሞክሮ "ሊሰጉ" እና "በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በሚሰጡ ማናቸውም የውሳኔ ሃሳቦች ላይ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል" ሲሉ የማሌዥያው የፖለቲካ ተንታኝ አዝሚ ሀሰን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።


ከ15 ዓመታት በፊት እ.ኤ.አ. መጋቢት 19፣ 2011ዓ.ም ኔቶ "ሰብአዊ ተልዕኮ" በሚል ሰበብ በሊቢያ ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት መክፈቱ ይታወሳል።

ሀሰን የሊቢያው ሁኔታ ተከስቶባቸው የነበሩ ወይም ሊደገምባቸው የሚችሉ የደቡባዊ ዓለም ሀገራትን እንደሚከተለው ይዘረዝራሉ፦

በነዳጅ የበለፀገችው ቬንዙዌላ፦ የመንግሥት ግልበጣ ሙከራ ተካሂዶባታል፡፡

ኢራን፦ "ቀጣዩ ተራ የእሷ ሊሆን ይችላል"

ሶሪያ፣ ኢራቅ እና አፍጋኒስታን፦ በእነዚህ ሦስት ሀገራት የኔቶ ብቸኛ ፍላጎት "የተፈጥሮ ሀብታቸው" እንጂ "ዲሞክራሲን ማስፈን" እንዳልነበረ ታይቶባቸዋል።

​የደቡባዊ ዓለም ሀገራት ከምዕራባውያን ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን ለመከላከል አማራጭ ስብስቦችን መፍጠር እንዳለባቸው የጠቀሱት ሀሰን፣ "ብሪክስ በፋይናንስ እና በጂኦፖለቲካዊ ጥምረት ረገድ የተሻለ አማራጭ መድረክ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ደምድመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0