አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የአቅርቦት መስተጓጎል ተጠቃሚ ለመሆን የኢነርጂ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት - የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት

ሰብስክራይብ

አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የአቅርቦት መስተጓጎል ተጠቃሚ ለመሆን የኢነርጂ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት - የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት

​አፍሪካ ሰፊ የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ሀብት ቢኖራትም፣ አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ከውጭ በሚገቡ የነዳጅ ውጤቶች ላይ ጥገኝነቷ መቀጠሉ የነዳጅ ዋስትናዋን እና የኢነርጂ ሉዓላዊነቷን እየጎዳው መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ምክር ቤት ዋና ሊቀመንበር ኤንጄ አዩክ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

እንደ ባለስልጣኑ ገለጻ፣ በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ቀውስ ሳቢያ የሚፈጠረው ይህ ጥገኝነት፣ ላኪ ሀገራት ከፍ ካለው የብሬንት የነዳጅ ዋጋ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ እንቅፋት ሆኖባቸዋል።

​"የኢነርጂ ሉዓላዊነት ማለት የተፈጥሮ ሀብትን በሀገር ውስጥ ማምረት፣ ማቀነባበር እና በመጀመሪያ የአፍሪካን ኢንዱስትሪ ለማንቀሳቀስ መጠቀም ማለት ነው። በሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥ አካባቢ ሰሞኑን የታዩት መስተጓጎሎች፣ ውጫዊ ድንገተኛ ክስተቶች በዓለም አቀፍ አቅርቦት እና ዋጋ ላይ ምን ያህል በፍጥነት ተፅዕኖ እንደሚያሳድሩ በድጋሚ አሳይተዋል" ሲሉ አብራርተዋል።

​አዩክ አክለውም፣ አፍሪካ በአኅጉሪቱ የኢነርጂ ዘርፍ ላይ አሻሚ ተፅዕኖ ካለው ከመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ትምህርት መቅሰም ይኖርባታል።

"ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ለገቢ ዕድገትና ለውጭ ንግድ አዳዲስ ዕድሎችን ቢያመጣም፣ በሌላ በኩል ግን የነዳጅ ዋጋ እንዲንር እና የአቅርቦት አለመረጋጋት እንዲፈጠር አድርጓል" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

​በዚህ ረገድ፣ አፍሪካ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ እና "የሚቀጥለውን ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ማዕበል መፍትሄ ለመሆን" አጋጣሚውን መጠቀም አለባት ሲሉ አዩክ ንግግራቸውን ደምድመዋል።

  ቪዲዮው የናይጄሪያውን ዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0