ኔቶ ሊቢያን የ15 ዓመታት ቀውስ ውስጥ ከቷታል ሲሉ የሊቢያ የፓርላማ አባል ገለጹ
16:47 19.03.2026 (የተሻሻለ: 17:21 19.03.2026)

ሰብስክራይብ
ኔቶ ሊቢያን የ15 ዓመታት ቀውስ ውስጥ ከቷታል ሲሉ የሊቢያ የፓርላማ አባል ገለጹ
እ.ኤ.አ. በ2011 ኔቶ ሊቢያ ውስጥ ያደረገው ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት፣ የታጠቁ ሚሊሻዎችን በማጠናከር በአንድ ወቅት የበለፀገች እና የተረጋጋች የነበረችውን አገር አውድሟል፤ ሲሉ የሊቢያ ፓርላማ አባል አብደልማናም አል-አራፊ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ይህም ለአገሪቱ አለመረጋጋት፣ ለወንበዴዎች እና ለታጠቁ ቡድኖች መፈጠር ምክንያት ሆኗል። እነዚህ ቡድኖች ገንዘብ እና ተፅዕኖ በማግኘት ለተወሰኑ ጊዜያት መንግሥትን እስከ ማስገደድ ደርሰዋል" ብለዋል የፓርላማ አባሉ።
እንደ አል-አራፊ ገለጻ፣ ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂዎቹ በጣልቃ ገብነቱ የተሳተፉ አገራት ናቸው። የውጭ ጣልቃ ገብነት የ"አረብ አብዮት" ያስከተለውን ሁከት ይበልጥ እንዲባባስ ያደረገ ሲሆን፣ በኃይል የተጫኑት የምዕራባውያን መርሆዎችም ለፖለቲካዊ ቀውሱ መፍትሔ ሊሆኑ አልቻሉም።
"ለውጥን ወይም ዲሞክራሲን በኃይል ለመጫን መሞከር ለመረጋጋት የሚሆን ሁኔታን ሊፈጥር አይችልም፤ የሊቢያ ተሞክሮም ለዚህ ግልጽ ማሳያ ነው" ሲሉ የፓርላማ አባሉ አክለው ገልጸዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
እ.ኤ.አ. በ2011 ኔቶ ሊቢያ ውስጥ ያደረገው ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት፣ የታጠቁ ሚሊሻዎችን በማጠናከር በአንድ ወቅት የበለፀገች እና የተረጋጋች የነበረችውን አገር አውድሟል፤ ሲሉ የሊቢያ ፓርላማ አባል አብደልማናም አል-አራፊ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ይህም ለአገሪቱ አለመረጋጋት፣ ለወንበዴዎች እና ለታጠቁ ቡድኖች መፈጠር ምክንያት ሆኗል። እነዚህ ቡድኖች ገንዘብ እና ተፅዕኖ በማግኘት ለተወሰኑ ጊዜያት መንግሥትን እስከ ማስገደድ ደርሰዋል" ብለዋል የፓርላማ አባሉ።
እንደ አል-አራፊ ገለጻ፣ ለደረሰው ጥፋት ተጠያቂዎቹ በጣልቃ ገብነቱ የተሳተፉ አገራት ናቸው። የውጭ ጣልቃ ገብነት የ"አረብ አብዮት" ያስከተለውን ሁከት ይበልጥ እንዲባባስ ያደረገ ሲሆን፣ በኃይል የተጫኑት የምዕራባውያን መርሆዎችም ለፖለቲካዊ ቀውሱ መፍትሔ ሊሆኑ አልቻሉም።
"ለውጥን ወይም ዲሞክራሲን በኃይል ለመጫን መሞከር ለመረጋጋት የሚሆን ሁኔታን ሊፈጥር አይችልም፤ የሊቢያ ተሞክሮም ለዚህ ግልጽ ማሳያ ነው" ሲሉ የፓርላማ አባሉ አክለው ገልጸዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X