ማስጠንቀቂያ፦ የሚረብሹ ምስሎችን
የናይጄሪያ ጦር ከ80 በላይ አሸባሪዎችን መደምሰሱ አስታወቀ
የእስላማዊ መንግሥት የምዕራብ አፍሪካ ግዛት (አይኤስደብሊውኤፒ)* የተባለው የሽብር ቡድን፣ በቦርኖ ግዛት ማላም ፋቶሪ በተባለ ስፍራ በናይጄሪያ ጦር ይዞታዎች ላይ የተቀናጀ ጥቃት ሰንዝሮ የነበረ ቢሆንም፣ ጥቃቱ በናይጄሪያ ወታደሮች በቆራጥነት መመከቱን ይፋዊ የወታደራዊ መግለጫ አረጋግጧል።
በ"ሀዲን ካይ" ስር ባሉ ጥምር ኃይሎች የተካሄደው ይህ ኦፕሬሽን፣ የቡድኑን ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦችን ጨምሮ በርካታ አማጺያንን መደምሰስ መቻሉን ዘገባው ገልጿል።
የናይጄሪያ ወታደራዊ ባለሥልጣናት የውጊያውን ውጤት የአሸባሪ ቡድኑን አቅም በከፍተኛ ሁኔታ ያዳከመ ነው ሲሉ ገልጸውታል።
"ይህ ወሳኝ ድል ለአሸባሪዎቹ መረብ ግዙፍ ውድቀት ሲሆን፣ በዘመቻው ቀጣና ውስጥ ያሉ የ'ሀዲን ካይ' ኃይሎች እያደገ የመጣውን የውጊያ ብቃት፣ ጽናት እና የታክቲክ የበላይነት ይበልጥ የሚያረጋግጥ ነው" ሲል ዘገባው ደምድሟል።
* በሩሲያ እና ሌሎች ሀገራት የታገደ የሽብር ድርጅት
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X