የቻድ መሪ የድሮን ጥቃትን ተከትሎ ከሱዳን ጋር የሚያዋስናቸው ድንበር ዘጉ

የቻድ መሪ የድሮን ጥቃትን ተከትሎ ከሱዳን ጋር የሚያዋስናቸው ድንበር ዘጉ
የቻድ መሪ የድሮን ጥቃትን ተከትሎ ከሱዳን ጋር የሚያዋስናቸው ድንበር ዘጉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.03.2026
ሰብስክራይብ
የቻድ መሪ የድሮን ጥቃትን ተከትሎ ከሱዳን ጋር የሚያዋስናቸው ድንበር ዘጉ

​የቻድ ፕሬዝዳንት ማሃማት ኢድሪስ ዴቢ ኢትኖ፣ "የበርካታ የቻድ ዜጎችን ሕይወት ለቀጠፈው" የድሮን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት አስቸኳይ የደህንነት ስብሰባ መጥራታቸውን የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

​እንደ አካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘገባ ከሆነ በጥቃቱ በትንሹ 17 ሰዎች ተገድለዋል።

​ፕሬዝዳንቱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር አላማዬ ሀሊና የመንግሥት ልዑካን ቡድን ወደ ስፍራው በመላክ የደረሰውን የሰው ሕይወት መጥፋት እና የንብረት ውድመት እንዲያጣሩ መመሪያ ሰጥተዋል።

​በተጨማሪም ብሔራዊ ጦሩ ከሱዳን በኩል ለሚሰነዘር ለማንኛውም ጥቃት አጸፋዊ እርምጃ እንዲወስድ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0