የኔቶ የሊቢያ ጣልቃ ገብነት "የታቀደ ወረራ" ነበር - ተንታኝ

የኔቶ የሊቢያ ጣልቃ ገብነት "የታቀደ ወረራ" ነበር
የኔቶ የሊቢያ ጣልቃ ገብነት የታቀደ ወረራ ነበር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.03.2026
ሰብስክራይብ
የኔቶ የሊቢያ ጣልቃ ገብነት "የታቀደ ወረራ" ነበር - ተንታኝ


"ኔቶ በሊቢያ ላይ የከፈተው ጦርነት የተፈጥሮ ሀብቷን ለመበዝበዝ እና 'የወርቅ ዲናር' የተሰኘውን የገንዘብ እቅድ ለማክሸፍ ያለመ የታቀደ የወረራ ወንጀል ነበር" ሲሉ ዓለም አቀፍ የሕግ ባለሙያ መሐመድ ማሕሙድ መህራን ለስፑትኒክ ተናግረዋል።


​ከአሥራ አምስት ዓመታት በኋላ፣ ምዕራባውያን "ንጹሐንን ለመጠበቅ" በሚል ያቀረቡት ምክንያት ሐሰት መሆኑ "በግልጽ የሚታወቅ" ነው ያሉት ባለሙያው፤ ጦርነቱ "የምዕራባውያንን የፋይናንስ የበላይነት" የተገዳደረችን አገር ለማፈራረስ የተደረገ ጥረት መሆኑን ገልጸዋል።


"ኔቶ ሊቢያን በአፍሪካ ከፍተኛ የኑሮ ደረጃ ከነበራት አገርነት፣ ወደ ትርምስና በእርስ በርስ ጦርነት ወደተዘፈቀች የፈረሰች አገር ቀይሯታል" ሲሉ መህራን አጽንኦት ሰጥተዋል።



የጣልቃ ገብነቱ እውነተኛ ዓላማዎች "ሙሉ በሙሉ ኢኮኖሚያዊ እና ጂኦ-ፖለቲካዊ" መሆናቸውን የጠቀሱት ባለሙያው፣ የሊቢያ ሁኔታ ሌሎች አገራት ለጦርነት የሚቀርቡ "ሰብአዊ" ምክንያቶችን በጥንቃቄ እንዲመለከቱ "ከባድ ትምህርት" የሰጠ ነው ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0