ጋና አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ አለባት፦ የቀድሞ ሚኒስትር በኢራን ቀውስ ምክንያት ሊከሰት ለሚችለው ተጽዕኖ አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ
11:07 19.03.2026 (የተሻሻለ: 11:14 19.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጋና አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ አለባት፦ የቀድሞ ሚኒስትር በኢራን ቀውስ ምክንያት ሊከሰት ለሚችለው ተጽዕኖ አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቁ
የቀድሞው የመሬት እና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር ሳሙኤል አቡ ጂናፖር፣ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሰነዘሩትን ጥቃት ተከትሎ ሊከሰት የሚችለውን ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ለመመካከር ፕሬዝዳንት ማሃማ አስቸኳይ የካቢኔ ስብሰባ እንዲጠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ጋና ዜጎቿን ከሚደርስባቸው ጫና ለመታደግ፣ በተለይም የፔትሮኬሚካል ዘርፉ አደጋ ላይ ባለበት ወቅት በፍጥነት እርምጃ መውሰድ እንዳለባት አሳስበዋል። ሌሎች አገራት አስቀድመው ወሳኝ እርምጃዎችን እየወሰዱ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
ጂናፖር በተጨማሪም፣ የአኩፎ-አዶ አስተዳደር እንደ የጎርጎሮሳውያኑ 2008ቱ የኢኮኖሚ ውድቀት እና የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ያሉ ያለፉ ቀውሶችን የተቆጣጠረበትን መንገድ በማድነቅ፣ አሁንም ተመሳሳይ ፈጣን እርምጃ እንዲወሰድ አሳስበዋል።
የቀድሞው ሚኒስትር ያሉትን ዝርዝር ተጨማሪ ጉዳዮች ለማወቅ በጋና ዘጋቢያን ኒማቱ ያኩቡ አቱዬሴ የተጠናቀረውን ቪዲዮ ይመልከቱ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X