ደቡብ ሱዳን በኢራን ላይ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ከጨመረው የነዳጅ ዋጋ ተጠቃሚ ሆናለች - የሃገሪቱ ባለሥልጣን
18:43 18.03.2026 (የተሻሻለ: 19:14 18.03.2026)
ሰብስክራይብ
ደቡብ ሱዳን በኢራን ላይ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ከጨመረው የነዳጅ ዋጋ ተጠቃሚ ሆናለች - የሃገሪቱ ባለሥልጣን
ደቡብ ሱዳን ወደ ለየለት የእርስ በርስ ጦርነት የመመለስ እድሏ አነስተኛ መሆኑን የጆንግሌ ግዛት መንግሥት ሚኒስትር ዱንጋ ጋይ ዱንጋ ኮለር ለስፑትኒክ ተናግረዋል። ሚኒስትሩ በተለያዩ ሪፖርቶች የሚወጡ ማስጠንቀቂያዎች ነባራዊ ሁኔታውን እንደማያንጸባርቁም ጠቁመዋል።
ምንም እንኳን አልፎ አልፎ በጎሳ እና በፖለቲካ ምክንያት የሚፈጠሩ ግጭቶች ቢቀጥሉም፣ በሀገር ውስጥ የግጭት አፈታት ሂደቶች መፍትሄ እያገኙ መሆናቸውንና አገሪቱ አሁን ሥራ ላይ ያለ መንግሥት፣ አመራር እና የሰላም ስምምነት እንዳላት ገልጸዋል።
መንግሥት በደቡብ ሱዳን ሕዝባዊ ነፃነት ንቅናቄ ቁጥጥር ስር ያሉ አካባቢዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ዓላማ ያለው ሲሆን፣ በዚህ ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የውጭ አካል ጣልቃ ገብነት እንደሌለበት ሚኒስትሩ አክለው አስረድተዋል።
የአሜሪካና የኢራን ጦርነት በደቡብ ሱዳን የሰላም ሂደት ላይ ትኩረት እንዲቀነስ አድርጎ እንደሆነ ሲጠየቁ፣ ኮለር ግጭቱ ምንም ዓይነት ቀጥተኛ የፖለቲካ ተፅዕኖ የለውም ያሉ ሲሆን፣ ይሁን እንጂ በኢኮኖሚ በኩል አገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየጨመረ ከመጣው የነዳጅ ዋጋ ተጠቃሚ መሆኗን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን በተለይ በወታደራዊ እና በደህንነት ዘርፎች ፈተናዎች ቢኖሩም፣ የተቀሩት የሰላም ስምምነቱ ድንጋጌዎች አተገባበር መቀጠሉን አስረድተዋል።
በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ጁባ የሰላም መንገዱን እንደማትተወው ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል። ይህም ደህንነትን፣ መረጋጋትን እና ማህበራዊ ጥምረትን ለማጠናከር እንዲሁም ሁከትን ውድቅ ለማድረግ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑን ጠቁመዋል። ማንኛውም ሀገር ያለ ሰላም እና ደህንነት ቀጣይነት ያለው ልማትና መረጋጋት ማምጣት እንደማይችልም አሳስበዋል።
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X