ጊኒ፣ ላይቤሪያ እና ሴራሊዮን የድንበር ደህንነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
13:15 18.03.2026 (የተሻሻለ: 13:24 18.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጊኒ፣ ላይቤሪያ እና ሴራሊዮን የድንበር ደህንነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
በኮናክሪ በተካሄደው የሦስትዮሽ የመሪዎች ጉባኤ ላይ፣ መሪዎቹ በጋራ ድንበሮቻቸው ላይ የሚታዩ የግጭት መንስኤዎችን መመርመራቸውንና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን እንዲሁም ቀጣናዊ አሰራሮችን መሰረት ባደረገ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ቃል መግባታቸውን የጊኒ ፕሬዝዳንት ማማዲ ዱምቡያ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
መሪዎቹ የደህንነት ትብብራቸውን በሚከተሉት መንገዶች ለማጠናከር ተስማምተዋል፦
በድንበር አካባቢዎች የጋራ ጥበቃን ማጠናከር፣
የመረጃ ልውውጥ ማድረግ እና
በአካባቢው ባለሥልጣናት እና በደህንነት ኃይሎች መካከል ፈጣን የኮሙኒኬሽን ስርዓት መዘርጋት።
"ውጥረቶችን ለመከላከል፣ ውይይትን ለማቀላጠፍ እንዲሁም የየብስ እና የባህር ድንበሮችን የመለየትና የመከለል ሥራን ለማስቀጠል የድንበር ጉዳዮች የሚመለከታቸው የቴክኒክ ክፍሎች በአስቸኳይ እንዲገናኙ መመሪያ ተሰጥቷል" ሲል ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/