የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት፦ የመላው ቀጣናው አሁናዊ መረጃዎች
የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት፦ የመላው ቀጣናው አሁናዊ መረጃዎች
⭕ ኢራን የከፍተኛው ብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ጸሐፊ አሊ ላሪጃኒ መገደላቸውን አረጋግጣለች። ግድያው የተፈጸመው ምክትላቸውን፣ ሴት ልጃቸውን፣ ወንድ ልጃቸውን እና በርካታ የደህንነት ጠባቂዎቻቸውን ጭምር ባካተተ መልኩ ነው።
⭕ በቤይሩት፣ ባሹር በተባለ ሰፈር ውስጥ የሚገኝ የመኖሪያ ህንፃ በጦር አውሮፕላን ተመትቶ የሦስት ሰዎች ህይወት አልፏል።
⭕ በባግዳድ፣ በአሜሪካ ኤምባሲ ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት ፍንዳታ ተከስቷል።
⭕ የኢራን አብዮታዊ ዘብ፣ "የእውነተኛ ቃል ኪዳን ኦፕሬሽን 4" ስር ከማዕበል 58-61 የሚደርሱ አዳዲስ መጠነ ሰፊ ቀጣናዊ ጥቃቶችን ማካሄዱን አስታውቋል፦
ማዕበል 58፦ በህፃናት ሰማዕታት ስም የተሰየመ ሲሆን፣ "ክሆራምሻህር" የተባሉ እጅግ ከባድ ሚሳኤሎችን በመጠቀም በሰሜንና በመካከለኛው እስራኤል እንዲሁም የ5ኛው የባህር ሃይል ጦር ሰፈርን ጨምሮ በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ተፈጽሟል።
ማዕበል 59፦ ቴል አቪቭን፣ እየሩሳሌምን እንዲሁም በአል ኡደይድ፣ ኤርቢል እና ሼክ ኢሳ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮችን ኢላማ አድርጓል።
ማዕበል 60፦ በቀጣናው በጠቅላላ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች፣ በእስራኤል የአሽዶድ የነዳጅ ማደያ ማዕከል እና በራፋኤል ወታደራዊ ኮምፕሌክስ ላይ ጥቃት ሰንዝሯል።
ማዕበል 61፦ ለላሪጃኒ ግድያ አጸፋ ለመመለስ በቴል አቪቭ ላይ መጠነ ሰፊ የሚሳኤል ጥቃት ተከፍቷል። በክሆራምሻህር-4፣ ቃድር፣ ኢማድ እና ኬይባር ሸካን ሚሳኤሎች የታገዘው ይህ ጥቃት የእስራኤልን የአየር መከላከያ ሰብሮ በመግባት ከ100 በላይ ወታደራዊ ኢላማዎችን መምታቱ ተገልጿል። እንደ አብዮታዊ ዘብ መረጃ፣ የከተማዋ የተወሰኑ ክፍሎች ከጥቅም ውጭ የሆኑ ሲሆን ከ230 በላይ እስራኤላውያን ተገድለዋል ወይም ቆስለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X