ብሪክስ በዚህ የጂኦፖለቲካዊ ቀውስ ወቅት ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ ሥርዓትን የመምራት ዕድል አለው - ደቡብ አፍሪካዊ ተመራማሪ
10:37 18.03.2026 (የተሻሻለ: 10:44 18.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ብሪክስ በዚህ የጂኦፖለቲካዊ ቀውስ ወቅት ፍትሐዊ ዓለም አቀፍ ሥርዓትን የመምራት ዕድል አለው - ደቡብ አፍሪካዊ ተመራማሪ
ሚካቴኪሶ ኩባዪ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደገለጹት፣ ጥምረቱ ምንጊዜም ቢሆን የበላይነትን ሳይሆን ማሻሻያን ሲደግፍ ቆይቷል። "ይህ ለብሪክስ የመሪነት ሚናን ለመያዝ የተመቻቸ ዕድል ነው።"
በተመሳሳይ ጊዜ፣ የምዕራባውያን ድርጊቶች ተዓማኒነታቸውን እንደሸረሸረው በመጥቀስ "ማንኛውም የሞራል የበላይነት ተሟጧል" ሲሉ ሞግተዋል።
ኩባዪ አክለውም፣ የአፍሪካ እና የእስያ አገራት ሉዓላዊነታቸውን ለመጠበቅ ሲሉ ከአንድ ወገን ጋር ብቻ ከመወገን እየተቆጠቡ መሆኑንና ለአማራጭ የፋይናንስ ሥርዓቶች ያላቸው ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
"የብሪክስ ድንበር-ተሻጋሪ የክፍያ ሥርዓት ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ ይሆናል" ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ይሁን እንጂ፣ ከፍተኛ የብድር ወለድ እና ደካማ የኢንቨስትመንት ፍሰት አሁንም ዋና እንቅፋቶች መሆናቸውንና ይህም አፍሪካ ከነዚህ ለውጦች ሙሉ በሙሉ ተጠቃሚ የመሆን አቅሟን እየቀነሰው መሆኑን አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X