'የጦርነት ውጤት በትዊተር መልዕክቶች አይወሰንም' ሲሉ የኢራን ኻተም አል-አንቢያ ዋና መሥሪያ ቤት ተወካይ ለትራምፕ ተናገሩ

ሰብስክራይብ

'የጦርነት ውጤት በትዊተር መልዕክቶች አይወሰንም' ሲሉ የኢራን ኻተም አል-አንቢያ ዋና መሥሪያ ቤት ተወካይ ለትራምፕ ተናገሩ

​በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን ግጭት ዙሪያ ያሉ ወቅታዊ መረጃዎች፦

የኢራን ብሔራዊ ደህንነት ጠቅላይ ምክር ቤት ጸሐፊ እንደገለጹት፣ የኢራን ሕዝብ በ"ኤፕስታይን ደሴት" ትርፍራፊዎች ላይ የሚያገኘው ታሪካዊ ድል ቀርቧል።

ኢራን በእስራኤል በተገደሉት የሀገሪቱ የብሔራዊ ደህንነት ጠቅላይ ምክር ቤት ጸሐፊ አሊ ላሪጃኒ መተካታቸውን አስታውቃለች፡፡

ቀደም ሲል፣ ኢራን ለላሪጃኒ ሞት አጸፋ እስራኤል ላይ 61ኛ ዙር ጥቃት ይፋ አድርጋለች፡፡

የኻተም አል-አንቢያ ማዕከላዊ ዕዝ ዋና መሥሪያ ቤት ተወካይ፣ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚገኘው የአሜሪካው አል ዳፍራ ወታደራዊ ካምፕ በኢራን ጦር ኃይል ጥቃት ከተፈፀመበት በኋላ የማጥቃት አቅሙ በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል ብለዋል።

የኢራን ጦር ተወካይ፣ ጠላት ዳግመኛ ጥቃት ለመሰንዘር እንዳይደፍር ኢራን አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ አለባት ሲሉ ተናግረዋል።

የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ፣ የጠላት ድሮኖች ምንም ያህል የተራቀቁ ቢሆኑም ኢራን እንደምትደመስሳቸው ገልጸዋል።

የኢራን ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዜሽኪያን፣ ሕዝቡ ጥቃት በተፈፀማባት"የዴና" መርከብ ወታደራዊ አባላት የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ በነቂስ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ትራምፕ የሆርሙዝ የባሕር ወሽመጥን ለማስከፈት አሜሪካ የኔቶ እርዳታ አያስፈልጋትም ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0