- Sputnik አፍሪካ, 1920
Sovereignty Sources
ዓለም በሉላዊነት ምክንያት ስትተሳሰር ፤ ፕሮግራሙም አፍሪካ ባላት እምቅ የተፈጥሮ ኃብት፣ በማደግ ላይ ባለው የሕዝብ ቁጥሯ ፣ በወጣት ኃይሏ እና በአህጉሪቱ ባሉ አዳዲስ ግኝቶችና የመፍትሄ ሃሳቦች ያላትን የመወዳደር አቅምና ጥቅም በሰፊው ይዳስሳል፡፡ እንኳን ወደ 'ሶቨርኒቲ ሶርስ' ፕሮግራም በደህና መጡ፣

የሆርሙዝ ሰርጥ በደቡባዊ ዓለም ሀገራት ዓይን ሲቃኝ

የሆርሙዝ ሰርጥ በደቡባዊ ዓለም ሀገራት ዓይን ሲቃኝ
ሰብስክራይብ

''የኢነርጂ ዋጋ እየተመነጠቀ ነው፣ ተፅዕኖውንም እያስተዋልን ነው፤ የደቡባዊ ዓለም ሀገራት ከዓለም ፖለቲካ ትይዩ የሆነ ስርዓት መፍጠር ይኖርባቸዋል — የደቡባዊ ዓለም ሀገራት ድምፅ የሚሆናቸው ያስፈልጋቸዋል፣ በዚህም የስፑትኒክ አፍሪካ ጥረት የሚደነቅ ነው።'' ሲል ቀጠናዊና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮችን የሚከታተለው ጋዜጠኛ ቢንያም ካሴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል።

ሦስት ጉዳዮች በምንዳስስበት የሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራማችን፣ በክፍል አንድ በኢራን ጦርነት የተዘጋው የሆርሙዝ ሰርጥ በደቡባዊ ዓለም ሀገራት ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖን ከጋዜጠኛ ቢንያም ካሴ ጋር ቃኝተነዋል። በክፍል ሁለት ስለአፍሪካ ከተሞች ዕድገት በፕላን እና ልማት ሚኒስቴር የቀድሞ ቴክኒካል አማካሪ ቤካ መገርሳ ጋር ተወያይተናል።
በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ከኃይል አቅርቦት አጣብቂኝ ውስጥ ሲገባ እንደታላቁ የህዳሴ ግድብ ያሉ ፕሮጀክቶች አማራጭ ምንጭ የመሆናቸውን ሚና በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ጋር ያደረግነው ቆይታም የፕሮግራሙ ሌላኛው አካል ነው።
ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበው ፕሮግራም ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ Apple PodcastsDeezer Spotify Podcast AddictPocket CastsAfripodsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0