አፍሪካ ከኢራን ጦርነት የሚመጡ የውጭ ኢነርጂ አቅርቦት እጥረቶችን ለመቋቋም ውስጣዊ ጥንካሬን መገንባት አለባት - ደቡብ አፍሪካዊ ተመራማሪ
20:29 17.03.2026 (የተሻሻለ: 20:34 17.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አፍሪካ ከኢራን ጦርነት የሚመጡ የውጭ ኢነርጂ አቅርቦት እጥረቶችን ለመቋቋም ውስጣዊ ጥንካሬን መገንባት አለባት - ደቡብ አፍሪካዊ ተመራማሪ
የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት መባባስ በተለይም የዋጋ ግሽበትን በመጨመር እና የመሠረታዊ ቁሳቁሶችን ዋጋ በማናር በአፍሪካ ላይ ከባድ የኢኮኖሚ መዘዝ ሊያስከትል እንደሚችል ሚካቴኪሶ ኩባዪ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
ተመራማሪው፣ "ይህ ትንኮሳ ሳይኖር የተጀመረና የምርጫ ውጤት የሆነ ጦርነት የሚያስከትለው ኢኮኖሚያዊ መዘዝ ከፍተኛ ይሆናል" ያሉ ሲሆን፤ ብዙ ሰዎች እንደ ምግብ እና ኤሌክትሪክ ያሉ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት ሊቸገሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
ኩባዪ አክለውም፣ አፍሪካውያን እርስ በርስ ያላቸው የንግድ ልውውጥ ዝቅተኛ በመሆኑ እና የሎጂስቲክስ መሰረተ ልማታቸው ደካማ በመሆኑ ምክንያት ነዳጅ ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ የአፍሪካ አገራት ይበልጥ ተጋላጭ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መፍትሔዎች ቢኖሩም አፋጣኝ ውጤት እንደማይሰጡም አስጠንቅቀዋል፡፡
“ኢንቨስትመንቶች ውጤት ለማምጣት ጊዜ ይወስዳሉ፤ ምክንያቱም በመጀመሪያ የማምረቻ ተቋማት መገንባት አለባቸው፣ ከዚያም ምርቱ መመረት መቻል አለበት።”
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X