የኬንያ መከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አመራሮች በኢትዮጵያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ጉብኝት አደረጉ
17:02 17.03.2026 (የተሻሻለ: 17:04 17.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኬንያ መከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አመራሮች በኢትዮጵያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ጉብኝት አደረጉ
ለልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያን ታሪካዊና አሁናዊ ግንኙነት፣ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ራዕይና ተልዕኮ፣ የመማር መስተማር ሂደቱ እንዲሁም ኮሌጁ ለሌሎች አገራትና ለመከላከያ ብቁ የሰው ኃይል በማፍራት ረገድ ያበረከተውን አስተዋፅኦና ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ አዛዥ ብርጋዲየር ጄነራል ዮሐንስ መኮንን፣ "ጉብኝቱ ለሁለቱ አቻ ኮሌጆች ልምድና እውቀት ለመጋራት የሚስችል እድል ይፈጥራል" ማለታቸውን መከላከያ ሠራዊት በማኅበራዊ ገጹ ላይ አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያና ኬንያ በአፍሪካ ቀንድ ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ደረጃ ከሰላምና መረጋጋት አንፃር ወሳኝ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙም አክለዋል።
የኬንያ መከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ምክትል ኮማንዳንትና የልዑካን ቡድኑ መሪ ብርጋዲየር ጄነራል ዴኬ ቼሲሬ በበኩላቸው፣ በመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ያደረጉት ጉብኝት እንደቀጣና የተካሄደ ትምህርታዊ ጉብኝት መሆኑን ገልፀው በጉብኝቱም ጠቃሚ ልምድና ተሞክሮ መቅሰም እንደተቻለ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/3
© telegram sputnik_ethiopia

2/3
© telegram sputnik_ethiopia

3/3
© telegram sputnik_ethiopia
1/3
© telegram sputnik_ethiopia
2/3
© telegram sputnik_ethiopia
3/3
© telegram sputnik_ethiopia