ናሚቢያ በማዳበሪያ ምርት ዘርፍ የሩሲያን ድጋፍ ትጠብቃለች – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
11:31 17.03.2026 (የተሻሻለ: 11:34 17.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናሚቢያ በማዳበሪያ ምርት ዘርፍ የሩሲያን ድጋፍ ትጠብቃለች – የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
በአፍሪካዊቷ ሀገር የማዳበሪያ ፋብሪካን የመገንባት ጉዳይ በ11ኛው የሁለትዮሽ የንግድ ፎረም ላይ መወያያ እንደነበር የናሚቢያ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ንግድ ሚኒስትሯ ሴልማ አሺፓላ-ሙሳቪ ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ ይህንን መግለጫ የሰጡት ሰኞ ዕለት በዊንድሁክ በተካሄደው 11ኛው የሁለትዮሽ የበይነ–መንግሥታት ጥምር ኮሚሽን ስብሰባ ላይ ነው።
እንደ እሳቸው ማብራሪያ፣ መሰል ፋብሪካ መገንባቱ፦
⭕ ከውጭ የሚገቡ የምግብ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት ይቀንሳል፡፡
⭕ የማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ይቆጥባል፡፡
⭕ ሀገሪቱን ለአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አባል ሀገራት ማዳበሪያም እና የምግብ ምርቶች ላኪነት ያሸጋግራታል፡፡
ቪዲዮ፦ በዊንድሁክ የተካሄደው የሩሲያ-ናሚቢያ የሁለትዮሽ የበይነ–መንግሥታት ጥምር ኮሚሽን ስብሰባ ወቅት በስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ የተቀረጸ ምስል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X