የሩሲያ የማዳበሪያ አምራች ኡራልኬም ወደብ አልባ የአፍሪካ ሀገራትን ለመድረስ ያለመ ዕቅድ ይፋ አደረገ
17:34 16.03.2026 (የተሻሻለ: 17:44 16.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ የማዳበሪያ አምራች ኡራልኬም ወደብ አልባ የአፍሪካ ሀገራትን ለመድረስ ያለመ ዕቅድ ይፋ አደረገ
ኡራልኬም የማዳበሪያ አቅርቦትን በማሳደግ እና ከአፍሪካ ጋር አጋርነትን በማጠናከር ዙሪያ በናሚቢያ በተዘጋጀ ፎረም ላይ መክሯል፡፡
የሩሲያ ማዳበሪያዎችን ወደ አፍሪካ በመላክ ረገድ ቁልፍ የሆነው ኡራልኬም ግሩፕ፤ እ.ኤ.አ መጋቢት 13 ቀን በዊንድሆክ በተካሄደው የናሚቢያ-ሩሲያ የንግድ ፎረም ላይ ተሳትፏል።
ኩባንያው ባወጣው መግለጫ መሠረት፤ በውይይቱ ላይ የተካተቱ ዋና ዋና ዕቅዶች የሚከተሉት ናቸው፦
◻ ማዳበሪያ ለሀገር ውስጥ አርሶ አደሮች ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን የአቅርቦት መረቦችን ማስፋፋት፣
◻ ወደብ የሌላቸውን የአፍሪካ ሀገራት ለመድረስ በናሚቢያ በኩል የሎጂስቲክስ መስመሮችን ማልማት።
ℹ ፎረሙ የአኅጉሪቱን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ ትኩረት በማድረግ፤ በሩሲያ እና በአፍሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር የመንግሥት እና የንግድ መሪዎችን ያሰባሰበ ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X