የኬንያ ከፍተኛ ዲፕሎማት በሩሲያ የመንግሥት የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ነው
10:41 16.03.2026 (የተሻሻለ: 10:44 16.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኬንያ ከፍተኛ ዲፕሎማት በሩሲያ የመንግሥት የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ነው
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ ከመጋቢት 6 እስከ 9 በሚያደርጉት ጉብኝት፤ ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ከታች የተዘረዘሩትን ጨምሮ በርካታ ቁልፍ ጉዳዮችን ይወያያሉ፦
በሩሲያ እና በኬንያ መካከል ያለው የተለመደ የወዳጅነት ግንኙነት ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ እና የወደፊት ተስፋዎች፣
የፖለቲካ ውይይቶችን እና በተለያዩ ዘርፎች ያሉ ግንኙነቶችን ለማጠናከር የሚወሰዱ ተግባራዊ እርምጃዎች፣
ለጋራ ተጠቃሚነት የሚበጁ የንግድ፣ የኢኮኖሚ እና የሰብዓዊ ግንኙነቶችን ማስፋፋት።
ሰርጌ ላቭሮቭ በ2023 ከወቅቱ የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አልፍሬድ ንጋንጋ ሙቱዋ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ በናይሮቢ ውይይት አካሂደዋል። በወቅቱም የሁለትዮሽ የንግድ ትስስርን እና የፖለቲካ ትብብርን ለማሳደግ ተስማምተው ነበር።
ቪዲዮ፦ ሙዳቫዲ በየካቲት ወር ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X