ዚምባብዌ ሁሉን አቀፍ ልማት ላይ ያነጣጠረ የ2026-2030 ብሔራዊ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
18:50 14.03.2026 (የተሻሻለ: 19:04 14.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዚምባብዌ ሁሉን አቀፍ ልማት ላይ ያነጣጠረ የ2026-2030 ብሔራዊ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ስትራቴጂ ይፋ አደረገች
ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋጓ፤ የሀገሪቱን ዲጂታል ነፃነት እና ልማት ለማረጋገጥ የተወሰደ ወሳኝ እርምጃ ሲሉ በፓርላማ በተካሄደው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ገልጸዋል።
መርሐ-ግብሩ በአራት ዋና ዋና መርሆዎች ላይ የተመሠረተ ነው፦
የችሎታ እና የአቅም ግንባታ ልማት፣
የመሠረተ-ልማት ሉዓላዊነት፣
የሰው ሠራሽ አስተውህሎት አጠቃቀምን ማስፋፋት፣
ሥነ-ምግባራዊ አስተዳደር።
ፕሬዝዳንት ምናንጋጓ፤ አዲሱ ስትራቴጂ የትምህርት ሥርዓቱን ለማሻሻል እና ምርምሮችን ለማፋጠን ያስችላል ሲሉ በማኅበራዊ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል። ይህም የፕሮጀክቱን ዋና ዓላማ ማለትም ግብርናን፣ ዘመናዊ የማዕድን ዘርፍን እና የጤና ምርመራን በማበልጸግ "ሰውን ማዕከል ያደረገ" የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ዕውን ያደርጋል ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/