በመጀመሪያው ሳምንት የመራጮች ምዝገባ ከ9 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተመዘገቡ
15:41 14.03.2026 (የተሻሻለ: 18:24 14.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በመጀመሪያው ሳምንት የመራጮች ምዝገባ ከ9 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ተመዘገቡ
ከየካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በተከናወነው የመራጮች ምዝገባ ከ9 ሚሊዮን 36ሺህ በላይ ዜጎች የመራጭነት ካርድ መውሰዳቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ አስታውቀዋል።
መራጮች በምርጫ ጣቢያዎች በአካል በመቅረብ እንዲሁም "ምርጫዬ" በተሰኘው ዘመናዊ መተግበሪያ አማካኝነት ምዝገባቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።
ሰብሳቢዋ አክለውም በጠቅላላ ካሉት 52ሺህ 773 የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ 6ሺህ 395 ጣቢያዎች ሥራ እንዳልጀመሩ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X